عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ رضي الله عنهما قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«إِنَّ اللَّهَ يُحِبُّ أَنْ تُؤْتَى رُخَصُهُ، كَمَا يُحِبُّ أَنْ تُؤْتَى عَزَائِمُهُ».

[صحيح] - [رواه ابن حبان]
المزيــد ...

ኢብኑ ዐባስ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ አሉ: የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ አሉ፦
"አላህ ግዴታ ያደረገው ሲተገበር እንደሚወደው፤ ያግራውም ሲተገበር ይወዳል።"

Sahih/Authentic. - [Ibn Hibbaan]

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን አላህ አምልኮና ህግጋቶቹን በማቅለል የደነገጋቸው ማግራሪያዎች ሲተገበሩ እንደሚወድ ተናገሩ። እንዲሁም አቅመ አዳምና ጤነኛ የሆኑ ሰዎች በተቸገሩ ሰዓት የደነገገላቸውን ማቅለያዎች ለምሳሌ፦ ጉዞ ላይ ሰላትን ማሳጠርና ሰላትን ሰብስቦ መስገድ ይመስል ሢፈጸሙም አላህ እንደሚወድ ተናገሩ። ይህም ልክ ግዴታ ያደረጋቸው ሢሰሩ (ተግባራዊ ሲደረጉ) እንደሚወደው ነው። ምክንያቱም አላህ ባግራውም ጉዳዮች ሆነ ግዴታ ባደረገው ጉዳዮች ላይ ትእዛዙ አንድ ነውና።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ጥራት የተገባው አላህ የደነገጋቸው ማግራሪያዎች ሲሰሩ መውደዱ አላህ በባሮቹ ላይ ያለውን እዝነት እንረዳለን።
  2. የዚህን ሸሪዐ ምሉእነትና በሙስሊም ላይ ችግርን ያነሳ መሆኑን እንረዳለን።