عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرِو بْنِ الْعَاصِ رضي الله عنهما قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«إِنَّ الْإِيمَانَ لَيَخْلَقُ فِي جَوْفِ أَحَدِكُمْ كَمَا يَخْلَقُ الثَّوْبُ الْخَلِقُ، فَاسْأَلُوا اللَّهَ أَنْ يُجَدِّدَ الْإِيمَانَ فِي قُلُوبِكُمْ».

[صحيح] - [رواه الحاكم والطبراني]
المزيــد ...

ዐብደላህ ቢን ዐምር ቢን አልዓስ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንዲህ አሉ፦ የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ አሉ፦
"ልክ ያረጀ ልብስ እንደሚደክመው ሁሉ ኢማንም በአንዳችሁ ልብ ውስጥ ይደክማል። አላህ ኢማንን በልባችሁ ውስጥ እንዲያድስ ለምኑት።"

Sahih/Authentic. - [Al-Haakim]

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን አዲስ ልብስን ለረጅም ጊዜ በመገልገላችን ምክንያት እንደሚደክም ሁሉ ኢማንም በሙስሊም ቀልብ ውስጥ እንደሚደክምና እንደሚያረጅ ተናገሩ። ይህም አምልኮ መፈፀምን በማቋረጥ ወይም ወንጀልን በመፈፀምና በስሜት ውስጥ በመዘፈቅ ምክንያት ነው። ስለዚህ ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን ግዴታ ነገሮችን በመፈፀም፣ ውዳሴና ምህረት መለመንን በማብዛት አላህ ኢማናችንን እንዲያድስልን እንድንለምነው ጠቆሙን።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ፅናት እንዲሰጠንና በቀልባችን ውስጥ ኢማንን እንዲያድስልን አላህን በመጠየቅ ላይ መነሳሳቱ ፤
  2. ኢማን ንግግርም ተግባርም እምነትም ሲሆን በአምልኮ (የአላህን ትዕዛዛት በመፈፀም) ሲጨምር በወንጀል ደግሞ ይቀንሳል።
ተጨማሪ