عن عمران بن حصين رضي الله عنه قال: كَانَتْ بِي بَوَاسِيرُ، فَسَأَلْتُ النَّبِيَّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ عَنِ الصَّلَاةِ، فَقَالَ:
«صَلِّ قَائِمًا، فَإِنْ لَمْ تَسْتَطِعْ فَقَاعِدًا، فَإِنْ لَمْ تَسْتَطِعْ فَعَلَى جَنْبٍ».

[صحيح] - [رواه البخاري]
المزيــد ...

ከዒምራን ቢን ሑሰይን -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አለ: "ኪንታሮት ነበረብኝና ስለ አሰጋገዴ ነቢዩን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ጠየቅኳቸው። እሳቸውም እንዲህ አሉኝ:-
'ቁመህ! ካልቻልክ ተቀምጠህ ካልቻልክ በጎንህ ተጋድመህ ስገድ። '"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]

ትንታኔ

መቆም ባልተቻለበት ወቅት ካልሆነ በቀር ለሶላት አሰጋገድ መሰረቱ መቆም እንደሆነና መቆም ካልቻለ ተቀምጦ እንደሚሰግድ ተቀምጦ መስገድም ካልቻለ በጎኑ ተጋድሞ መስገድ እንደሚችል ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ገለፁ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በአቅም ልክ ከሁኔታ ወደ ሁኔታ መሸጋገር እንጂ አይምሮ ጤነኛ እስከሆነ ድረስ ሶላት የማትቀር ግዴታ ናት።
  2. አንድ ሰው አምልኮን የሚፈፅመው በአቅሙ ልክ መሆኑ የኢስላምን ገርነትና ቀላልነትን ያስረዳናል።
ተጨማሪ