+ -

«مَنْ قَرَأَ آيَةَ الْكُرْسِيِّ فِي دُبُرِ كُلِّ صَلَاةٍ مَكْتُوبَةٍ لَمْ يَمْنَعْهُ مِنْ دُخُولِ الْجَنَّةِ إِلَّا أَنْ يَمُوتَ».
[صحيح] - [رواه النسائي في الكبرى]
المزيــد ...

ከአቡ ኡማማ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"ከሁሉም ግዴታ ሶላት በኋላ አየተል ኩርሲይን የቀራ ሰው ጀነት ለመግባት ከሞት በቀር ምንም አይከለክለውም።"»

ሶሒሕ ነው። - [At-Tabaraani]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ግዴታ ሶላት ከተጠናቀቀ በኋላ አየቱል ኩርሲይን የቀራ ሰው ከሞት በቀር ጀነት ለመግባት ምንም እንደማይከለክለው ተናገሩ። ይህቺም አንቀጽ በበቀራ ምእራፍ ውስጥ የምትገኝ ሲሆን እርሷም ይህቺ የአላህ ቃል ናት: ትርጉሟ: {አላህ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም። ህያው ራሱን ቻይ ነው። ማንገላጀትም እንቅልፍም አትይዘውም። በሰማያት ውስጥና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የርሱ ብቻ ነው። ያ እርሱ ዘንድ በፍቃዱ ቢሆን እንጂ የሚያማልደው ማነው? (ከፍጡሮች) በፊታቸው ያለውንና ከኋላቸው ያለውን ሁሉ ያውቃል። በሻውም ነገር እንጂ ከእውቀቱ በምንም ነገር አያካብቡም። (አያውቁም)። መንበሩ ሰማያትንና ምድርን ሰፋ። ጥበቃቸውም አያቅተውም። እርሱም የሁሉ በላይ ታላቅ ነው።} [አልበቀራህ: 255]

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ السويدية القيرقيزية اليوروبا الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ይህቺ ታላቅ አንቀፅ የአላህን ውብ ስሞችና የላቁ ባህሪያቱን በማካተቷ ያላትን ትሩፋት እንረዳለን።
  2. ይህቺን ታላቅ አንቀፅ ከሁሉም ግዴታ ሶላቶች በኋላ መቅራት ተወዳጅ መሆኑን እንረዳለን።
  3. መልካም ስራዎች ጀነት ለመግባት ሰበብ እንደሆኑ እንረዳለን።
ተጨማሪ