ምድቡ:
+ -

عَنْ أَبِي مُـحَمَّدٍ الحَسَنِ بْنِ عَلِيِّ بْنِ أَبِي طَالِبٍ - سِبْطِ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ وَرَيْحَانَتِهِ-، قَالَ: حَفِظْتُ مِنْ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«دَعْ مَا يَرِيبُك إلَى مَا لَا يَرِيبُكَ».

[صحيح] - [رواه الترمذي والنسائي] - [الأربعون النووية: 11]
المزيــد ...

የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- የልጅ ልጅና መአዛቸው ከሆነው ከአቡ ሙሐመድ ሐሰን ቢን ዓሊይ ቢን አቢጧሊብ እንደተላለፈው እንዲህ አለ: «ከአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ይህንን ሸምድጃለሁ:
"የሚያጠራጥርህን ነገር ተውና ወደ ማያጠራጥርህ ሂድ!"

[ሶሒሕ ነው።] - [رواه الترمذي والنسائي] - [الأربعون النووية - 11]

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ክልክል ነው ወይስ አይደለም፣ ሐላል ነው ወይስ ሐራም ነው እያልክ የምትጠራጠርበት ንግግርና ተግባር በመተው መልካምነቱንና ፍቁድነቱን እርግጠኛ ወደሆንክበትና ወዳልተጠራጠርክበት መሄድን አዘዙ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሙስሊም የሆነ ሰው ጉዳዮቹን በርግጠኝነት ላይ መመስረት አለበት። የሚጠራጠርበትን ነገር ትቶ በሃይማኖቱም እውቀት ላይ መሆን አለበት።
  2. አጠራጣሪ ነገር ላይ ከመውደቅ መከልከሉን እንረዳለን።
  3. እርጋታና እረፍትን ከፈለግክ አጠራጣሪ ነገርን ትተህ ወደ ጎን መጣል አለብህ።
  4. አላህ ለባሮቹ ነፍሳቸውና ሀሳባቸው እረፍት የሚያገኝበትን ማዘዙና ጭንቀትና መዋለል ውስጥ ከሚከታቸው ነገርም መከልከሉ ለነርሱ ያለውን እዝነት ያስረዳናል።
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ الغوجاراتية Kyrgyzisht النيبالية الليتوانية الدرية الصربية الطاجيكية Kinjaruandisht المجرية التشيكية الموري Kannadisht الولوف Azerisht الأوزبكية الأوكرانية الجورجية المقدونية الخميرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ምድቦች
ተጨማሪ