+ -

عَنْ أَنَسٍ رَضيَ اللهُ عنهُ قَالَ:
ضَحَّى النَّبِيُّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ بِكَبْشَيْنِ أَمْلَحَيْنِ أَقْرَنَيْنِ، ذَبَحَهُمَا بِيَدِهِ، وَسَمَّى وَكَبَّرَ، وَوَضَعَ رِجْلَهُ عَلَى صِفَاحِهِمَا.

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 5565]
المزيــد ...

ከአነስ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል:
«ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለኡዱሒያ ሁለት ቡራቡሬና ቀንዳም የሆኑ ሙክቶችን በእጃቸው አረዱ። "ቢስሚላህ አላሁ አክበር" አሉና እግራቸውን አንገቱ ላይ አድርገው አረዱት።»

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 5565]

ትንታኔ

አነስ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የዒድ አልአድሓ ቀን በእጃቸው ሁለት ቀንዳሞችና ጥቁር የተቀላቀለባቸው ነጫጭ ወንድ ሙክት በጎችን "ቢስሚላህ አላሁ አክበር" በማለት እግራቸውን አንገታቸው ላይ አድርገው እንዳረዱ ተናገረ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ኡዱሒያ የተደነገገ እንደሆነ እንረዳለን። በዚህም ጉዳይ ዑለሞች ባጠቃላይ ተስማምተዋል።
  2. ኡዱሒያው ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ያረዱት አይነት መሆኑ በላጭ ነው። ይህም ሲታይ ስለሚያምርና ሞራውና ስጋውም ጣፋጭ ስለሚሆን ነው።
  3. ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: «በዚህ ሐዲሥ አንድ ሰው ኡዱሒያውን በራሱ ማረድ እንደሚገባና በቂ ምክንያት ሳይኖረው ለማረድ ሰው መወከል እንደሌለበት እንረዳለን። በቂ ምክንያት ካለው ግን ሲታረድ መገኘቱ ይወደድለታል። በርሱ ፋንታ እንዲያርድለት ሙስሊም ሰው ከተካ ያለምንም ልዩነት ይፈቀዳል።
  4. ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «በዚህ ሐዲሥ ውስጥ በማረድ ወቅት ቢስሚላህ ከማለት ጋር አላሁ አክበር ማለት እንደሚወደድ፤ እግርን ደሞ በሚታረደው ቀኝ የአንገቱ ክፍል ላይ ማኖር እንደሚወደድ እንረዳለን። የሚታረደውን የምናስተኛው በግራ ጎኑ በመሆኑ ዑለሞች ተስማምተዋል። ለአራጁ ቢላን በቀኝ እጅ መያዝ፣ በግራ እጁ ደግሞ ጭንቅላቱን መያዝ እንዲቀለው እግሩን በሚታረደው እንስሳ ቀኝ አንገት ላይ ያደርጋል።
  5. ኡዱሒያ ቀንዳሙን ማረድ እንደሚወደድ እንረዳለን። ቀንድ ከሌለውም ግን ይፈቀዳል።