+ -

عَنْ عَبْدِ اللهِ بْنِ مَسْعُودٍ رَضيَ اللهُ عنهُ قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«لاَ تَتَّخِذُوا الضَّيْعَةَ فَتَرْغَبُوا فِي الدُّنْيَا».

[حسن لغيره] - [رواه الترمذي وأحمد] - [سنن الترمذي: 2328]
المزيــد ...

ከዐብደላህ ቢን መስዑድ ረዲየሏሁ ዓንሁ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድለላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ብለዋል:
"መስካችሁ ላይ ሙጥኝ አትበሉ ዱንያን ትከጅላላችሁና።"»

[Hasan/Sound by virtue of corroborating evidence] - [ቲርሚዚና አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሱነን ቲርሚዚ - 2328]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- የአትክልትና የእርሻ (የስራ) መስክ ላይ ሙጥኝ ማለትን ከለከሉ። ይህም ዱንያን ለመከጀልና ከአኺራ ይልቅ ወደ ዱንያ እንዲዘነበል ከሚያደርጉ ምክንያቶች አንዱ ስለሆነ ነው።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ከአኺራ የሚያዞር በሆነ መልኩ ዱንያን ሙጥኝ ማለት መከልከሉን እንረዳለን።
  2. ሐዲሡ ውስጥ የተከለከለው ለመኖሪያ የሚሆን የገቢ ምንጭ መያዝ አይደለም። የተከለከለው ዱንያ ውስጥ መስመጥና አኺራን መርሳት ነው።
  3. ሲንዲይ እንዲህ ብለዋል: "በሐዲሡ የተፈለገው: አላህን ከማስታወስ ስለሚያዘናጋችሁ የስራ መስካችሁን በመያዝ አትስመጡ ማለት ነው።"
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ