عَنْ زَيْدِ بْنِ خَالِدٍ الجُهَنِيِّ رضي الله عنه أَنَّهُ قَالَ:
صَلَّى لَنَا رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ صَلَاةَ الصُّبْحِ بِالْحُدَيْبِيَةِ عَلَى إِثْرِ سَمَاءٍ كَانَتْ مِنَ اللَّيْلَةِ، فَلَمَّا انْصَرَفَ أَقْبَلَ عَلَى النَّاسِ، فَقَالَ: «هَلْ تَدْرُونَ مَاذَا قَالَ رَبُّكُمْ؟» قَالُوا: اللهُ وَرَسُولُهُ أَعْلَمُ، قَالَ: «أَصْبَحَ مِنْ عِبَادِي مُؤْمِنٌ بِي وَكَافِرٌ، فَأَمَّا مَنْ قَالَ: مُطِرْنَا بِفَضْلِ اللهِ وَرَحْمَتِهِ، فَذَلِكَ مُؤْمِنٌ بِي وَكَافِرٌ بِالْكَوْكَبِ، وَأَمَّا مَنْ قَالَ: بِنَوْءِ كَذَا وَكَذَا، فَذَلِكَ كَافِرٌ بِي وَمُؤْمِنٌ بِالْكَوْكَبِ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ዘይድ ቢን ኻሊድ አልጁሀኒይ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንዲህ አሉ፦
የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን በሑደይቢያ ምሽት የዘነበን ዝናብ አስከትለው የንጋትን ሰላት አሰገዱን። ሰላቱን ያጠናቀቁ ጊዜም ወደ ሰዎች በመዞር እንዲህ አሉ "ጌታችሁ ምን እንዳለ ታውቃላችሁን?" ሰሓቦችም "አላህና መልክተኛው ያውቃሉ" አሉ። እርሳቸውም አላህ እንዲህ አለ፦ "ከባሮቼ በኔ ያመነም የካደም ሆኖ ያነጋ አለ። በአላህ ችሮታና እዝነት ምክንያት ዘነበልን ያለ በኔ ያመነ በከዋክብት የካደ ነው። በእንዲህ እንዲህ የኮኮብ እንቅስቃሴ ምክንያት ዘነበልን ያለ ደግሞ በኔ የካደና በከዋክብት ያመነ ነው።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን በሑደይቢያ (መካ አቅራቢያ የምትገኝ መንደር ናት) የንጋት (የሱቢሕ) ሰላትን በዛ ምሽት ዝናብ ከዘነበ በኋላ አሰገዱ። ሰላቱን በማሰላመት ያጠናቀቁ ጊዜ ፊታቸውን ወደ ሰዎች በመዞር "የተከበረውና የላቀው ጌታችሁ ምን እንዳለ ታውቃላችሁን?" በማለት ጠየቋቸው። ሰሓቦችም አላህና መልክተኛው ያውቃሉ በማለት መለሱላቸው። እርሳቸውም እንዲህ አሉ፦ " ከፍ ያለው አላህ ሰዎች ዝናብ በሚዘንብ ወቅት ለሁለት እንደሚከፈሉ ገለፁ። አንዱ ክፍል በአላህ አማኝ የሆነ ክፍል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በአላህ ከሀዲ የሆነ ክፍል ነው።" በአላህ ችሮታና እዝነት ዘነበልን በማለት የዝናብን መውረድ ወደ አላህ ያስጠጋ ሰው ይህ ፈጣሪና የዩንቨርሱ አስተናባሪ በሆነው አላህ ያመነ በከዋክብት ደግሞ የካደ መሆኑን፤ በእንዲህ እንዲህ ኮኮብ ዘነበልን ያለ ደግሞ በአላህ የካደና በከዋክብት ያመነ መሆኑን ገለፀ። ይህ ክህደት የዝናብን መውረድ ወደ ከዋክብት ከማስጠጋቱ አንፃር ትንሹ ኩፍር ነው። ምክንያቱም አላህ በሸሪዐም ሆነ በውሳኔ ዝናብ ለመዝነብ ሰበብ አላደረገውምና ነው። የዝናብን መውረድና ሌሎች ምድራዊ ክስተቶችን ከዋክብት ለመውጣትና ለማረፍ (ለመውደቅ) ወደሚያደርጉት እንቅስቃሴ ያስጠጋና ከዋክብት ትክክለኛ አስተናባሪ መሆናቸውን ያመነ ትልቁን ክህደት የካደ ይሆናል።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ከዝናብ መውረድ በኋላ፦ በአላህ ችሮታና እዝነት ዘነበልን ማለት እንደሚወደድ።
  2. የዝናብ መውረድና ሌሎችን ፀጋዎች መፍጠሩንም ሆነ ማስገኘቱን ወደ ከዋክብት ያስጠጋ ትልቁን ክህደት የካደ ሲሆን ወደ ከዋክብት በሰበብ ደረጃ ካስጠጋ ደግሞ ትንሹን ክህደት የካደ ይሆናል። ምክንያቱም ሸሪዐዊም ሆነ ህዋሳዊ ሰበብ አይደለምና።
  3. አንድ ፀጋ በተካደ ጊዜ የክህደት ምክንያት ሲሆን፤ ተገቢ ምስጋና ከቀረበበት ደግሞ የኢማን ምክንያት ይሆናል።
  4. የሽርክን መዳረሻ ለመዝጋት ሲባል ወቅቱን ለመግለፅ ተፈልጎበት ቢሆን እንኳን "በእንዲህ ኮኮብ እንቅስቃሴ ምክንያት ዘነበልን" ማለት መከልከሉ፤
  5. ፀጋን በማምጣትና መአትን በመከላከል ረገድ ቀልብን በአላህ ላይ ማንጠልጠል ግዴታ መሆኑን ተረድተናል።
ተጨማሪ