+ -

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«مَنْ غَدَا إِلَى الْمَسْجِدِ أَوْ رَاحَ أَعَدَّ اللهُ لَهُ فِي الْجَنَّةِ نُزُلًا، كُلَّمَا غَدَا أَوْ رَاحَ».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح مسلم: 669]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
"ማለዳ ላይ ወይም ከቀትር በኋላ ወደ መስጂድ የሄደ ሰው ማልዶ በሄደና ከቀትር በኋላ በሄደ ቁጥር አላህ ለርሱ ጀነት ውስጥ መስተንግዶ ያዘጋጅለታል።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 669]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ለአምልኮም ይሁን ለእውቀት ወይም ከዚህ ውጪ ላሉ መልካም አላማዎች በመጀመሪያው የቀን ክፍልም ሆነ በመጨረሻው የቀን ክፍል በማንኛውም ወቅት መስጂድ የመጣ ሰው በቀኑ ክፍለ ጊዜ ውስጥ ወይም በሌሊቱ ክፍለ ጊዜ ውስጥ መስጂድ በመጣ ቁጥር አላህ ለርሱ ጀነት ውስጥ ስፍራና መስተንግዶ እንዳዘጋጀለት አበሰሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية Oromisht
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ወደ መስጂድ የመሄድ ትሩፋትን፣ በመስጂድ ውስጥ በጀመዓ መስገድን በመጠባበቅ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን። ከመስጂዶች የሚቀር ሰው ስንትና ስንት ፀጋ፣ ደረጃ፣ ምንዳና አላህ የርሱን ቤት ላሰቡ ያዘጋጀው መስተንግዶ ያመልጠዋል!
  2. ሰዎች ቤቶቻቸው የሚመጣን የሚያከብሩና ለርሱ ምግብ የሚያቀርቡ ከሆነ አላህም ተባረከ ወተዓላ ከፍጡራኑ የበለጠ እጅግ ቸር ነው። የርሱን ቤት ያሰበን ሰው ያከብረዋል፣ አላህ ለርሱም ትልቅና የላቀ መስተንግዶ ያዘጋጅለታል።
  3. ወደ መስጂድ ማልዶም ይሁን አርፍዶ በሄደ ቁጥር ለርሱ መስተንግዶ ስለሚዘጋጅለት ወደ መስጂድ በመሄድ መደሰትና መመኘት ይገባል።