عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ:
أَوْصَانِي خَلِيلِي صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ بِثَلاَثٍ: صِيَامِ ثَلاَثَةِ أَيَّامٍ مِنْ كُلِّ شَهْرٍ، وَرَكْعَتَيِ الضُّحَى، وَأَنْ أُوتِرَ قَبْلَ أَنْ أَنَامَ.
[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 1981]
المزيــد ...
ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፦
"ፍፁም ወዳጄ የሆኑት ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ሶስት ነገሮች ላይ አደራ ብለውኛል። ከሁሉም ወር ሶስት ቀናት በመጾም፣ የዱሓን ሁለት ረከዓ በመስገድና ከመተኛቴ በፊት ዊትር በመስገድ አደራ ብለውኛል።"
[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 1981]
አቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ተወዳጁና ባልደረባው የሆኑት ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በሶስት ነገሮች አደራ እንዳሏቸውና ቃልኪዳንም እንዳስገቧቸው ተናገሩ:
የመጀመሪያው: ከሁሉም ወር ሶስት ቀናትን መጾም ነው።
ሁለተኛው: በየቀኑ ሁለት ረከዓ ዱሓ መስገድ ነው።
ሶስተኛው: ከመተኛት በፊት ዊትር መስገድ ነው። ይህ ግን የሌሊቱ መጨረሻ ላይ አልነቃም ብሎ ለፈራ ነው።