+ -

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«لَا يَسْتُرُ عَبْدٌ عَبْدًا فِي الدُّنْيَا إِلَّا سَتَرَهُ اللهُ يَوْمَ الْقِيَامَةِ».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 2590]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፦
" አንድ ባሪያ የአንድን ባሪያ ነውር በዱንያ አይሸፍንም፤ የትንሳኤ ቀን አላህ ነውሩን የሚሸፍንለት ቢሆን እንጂ።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2590]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አንድ ሙስሊም የሙስሊም ወንድሙን ነውር የሚሸፍን ከሆነ አላህ የትንሳኤ ቀን የርሱን ጉዳይ የሚሸፍንለት መሆኑን ገለፁ። የስራ ክፍያ እንደስራው አይነት ነው። አላህ ነውሩን የሚሸፍንለት ነውሩንና ወንጀሉን ከተቀሰቀሱ ፍጡራን በመሸሸግ ነው። በዛ ወንጀል መተሳሰብና ለርሱ ማውሳቱን በመተውም ሊሆን ይችላል።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አንድ ሙስሊም ወንጀል በሰራ ጊዜ ከማውገዝ፣ ከመምከር፣ አላህን እንዲፈራ ከመገሰፅ ጋር ወንጀሉንም መሸሸግ እንደተደነገገ እንረዳለን። ወንጀልና አመፅን በግልፅ የሚሰሩ የጥፋትና ብልሽት ባለቤት ከሆኑ ግን ለነርሱ ወንጀላቸውን መሸሸግ ተገቢ አይደለም። ለነርሱ መሸሸግ የበለጠ ለወንጀል ያደፋፍራቸዋል። ስማቸውን መጥራት እንኳ አስፈላጊ ከሆነ እነርሱ ወንጀሉንና አመፁን ግልፅ ያወጡ ስለሆኑ የነርሱ ጉዳይ የሚወሰደው ወደ መሪዎች ነው።
  2. የሌሎችን ስህተት በመሸሸግ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  3. ከመሸሸግ ጥቅሞች መካከል: ወንጀለኛ ነፍሱን እንዲገመግምና ወደ አላህ እንዲመለስ የጥሞና ጊዜ መስጫ ነው። ነውርንና እንከንን ግልፅ ማውጣት ፀያፍን ከማሰራጨት የሚመደብ ነውና። ነውርን ማሰራጨት ማህበራዊ ድባብንም ያበላሻል፤ ሌሎችም ነውሩን እንዲሰሩት ያነሳሳል።