عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ رَضيَ اللهُ عنه عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أَنَّهُ قَالَ:
«اللهُمَّ لَا عَيْشَ إِلَّا عَيْشُ الْآخِرَهْ، فَاغْفِرْ لِلْأَنْصَارِ وَالْمُهَاجِرَهْ».
[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح مسلم: 1805]
المزيــد ...
ከአነስ ቢን ማሊክ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ብለዋል፦
"አላህ ሆይ! ከመጪው አለም ኑሮ ውጪ ኑሮ የለም። ለአንሷሮችና ሙሃጂሮች ማራቸው።"
[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 1805]
ነቢዩ - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - እውነተኛ ኑሮ በመጪው አለም በአላህ ውዴታ፣ እዝነትና ጀነት ውስጥ ያለው ነው እንጂ ሌላ ትክክለኛ ኑሮ እንደሌለ ተናገሩ። የዱንያ ኑሮ ተወጋጅ ነው። የመጪው አለም ኑሮ ዘውታሪና ቀሪ ነው። ቀጥለውም ነቢዩ - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - ምህረትን፣ መከበርንና መልካምነትን ለእነዚያ ነቢዩን - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - እና ሙሃጂሮችን ላስጠጉትና ገንዘባቸውን ላካፈሉት አንሷሮች በተጨማሪ የአላህን ውዴታና ችሮታ ፈልገው ሃገራቸውንና ገንዘባቸውን ትተው ለተሰደዱት ዱዓ አደረጉላቸው።