عَنْ سَعْدِ بنِ أبي وَقَّاصٍ رَضيَ اللهُ عنه قَالَ:
كُنَّا عِنْدَ رَسُولِ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَقَالَ: «أَيَعْجِزُ أَحَدُكُمْ أَنْ يَكْسِبَ، كُلَّ يَوْمٍ أَلْفَ حَسَنَةٍ؟» فَسَأَلَهُ سَائِلٌ مِنْ جُلَسَائِهِ: كَيْفَ يَكْسِبُ أَحَدُنَا أَلْفَ حَسَنَةٍ؟ قَالَ: «يُسَبِّحُ مِائَةَ تَسْبِيحَةٍ، فَيُكْتَبُ لَهُ أَلْفُ حَسَنَةٍ، أَوْ يُحَطُّ عَنْهُ أَلْفُ خَطِيئَةٍ».
[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 2698]
المزيــد ...
ከሰዕድ ቢን አቢ ወቃስ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላችውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ:
«የአላህ መልክተኛ - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - ዘንድ ነበርን። እንዲህም አሉን: "አንዳችሁ በየቀኑ አንድ ሺህ ምንዳ መሸመት ይሳነዋልን?" ከተቀመጡት ሰዎች መካከል አንድ ጠያቂ "እንዴት ነው አንዳችን አንድ ሺህ ምንዳ የሚሸመተው?" በማለት ጠየቃቸው። እርሳቸውም: "መቶ ጊዜ ተስቢሕ ካለ ለርሱ አንድ ሺህ ምንዳ ይፃፍለታል ወይም ከርሱ ላይ አንድ ሺህ ወንጀል ይሰረዝለታል።" በማለት መለሱ።»
[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2698]
ነቢዩ - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - ባልደረቦቻቸውን እንዲህ በማለት ጠየቁ: አንዳችሁ በየቀኑ አንድ ሺህ ምንዳ ማግኘት አይችልምን? እዛው ከተቀመጡት መካከል አንዱ "አንድ ሰው በቀላሉ በየቀኑ አንድ ሺህ ምንዳ እንዴት ሊያገኝ ይችላል?" በማለት ጠየቀ። እርሳቸውም "መቶ ጊዜ ሱብሓነላህ ይበል። በዚህም አንድ ሺህ ምንዳ ይፃፍለታል።" አሉ። አንድ መልካም ስራ በአስር ትባዛለችና። ወይም አንድ ሺህ ወንጀሉ ይራገፍለታል።