عَنْ مُصْعَبِ بْنِ سَعْدٍ قَالَ: رَأَى سَعْدٌ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ أَنَّ لَهُ فَضْلًا عَلَى مَنْ دُونَهُ، فَقَالَ النَّبِيُّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«هَلْ تُنْصَرُونَ وَتُرْزَقُونَ إِلَّا بِضُعَفَائِكُمْ».
[صحيح] - [رواه البخاري] - [صحيح البخاري: 2896]
المزيــد ...
ከሙስዐብ ቢን ሰዕድ እንደተላለፈው እንዲህ አለ: «ሰዕድ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ከሌሎች ሰዎች የበለጠ ደረጃ እንዳለው ተሰማው። ነቢዩም ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ አሉት:
"የምትረዱትና የምትቀለቡት በደካሞቻችሁ ሰበብ አይደለምን?"
[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪ ዘግበውታል። - ቲርሚዚ ዘግበውታል። - An-Nasaa’i - አቡዳውድ ዘግበውታል። - አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 2896]
ሰዕድ ቢን አቢ ወቃስ ረዺየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራውን ይውደድለትና - ራሱን በጀግንነትና በመሳሰሉት ምክንያት ከርሱ በታች ካሉ ደካማ ሰዎች የበለጠ አድርጎ አሰበ። ነቢዩም ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- "በደካሞቻችሁ፣ በነርሱ ዱዓ፣ ሶላትና ኢኽላስ ካልሆነ በቀር ትረዳላችሁን? ትቀለባላችሁን?" አሉ። አብዛኛው ጊዜ ደካማዎች ዱዓቸውን እጅግ ለአላህ አጥርተው፣ አምልኳቸውንም እጅግ ተመስጠው ነው የሚፈፅሙት። ይህም ቀልባቸው በዱንያ ጌጣጌጥ ከመንጠልጠል የፀዳ ስለሆነ ነው።