+ -

عَنْ أُمِّ حَبِيبَةَ رضي الله عنها زَوْجِ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالت: سَمِعْتُ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ:
«مَنْ حَافَظَ عَلَى أَرْبَعِ رَكَعَاتٍ قَبْلَ الظُّهْرِ وَأَرْبَعٍ بَعْدَهَا حَرَّمَهُ اللَّهُ عَلَى النَّارِ».

[صحيح] - [رواه أبو داود والترمذي والنسائي وابن ماجه وأحمد] - [سنن الترمذي: 428]
المزيــد ...

የነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ባለቤት ከሆነችው ከኡሙ ሐቢባ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው እንዲህ አለች: «የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ:
"ከዝሁር በፊት አራት ረከዓዎች ላይና ከዝሁር በኋላ አራት ረከዓዎች ላይ የተጠባበቀ ሰው አላህ እሳትን በርሱ ላይ እርም አድርጎለታል።"»

[ሶሒሕ ነው።] - - [ሱነን ቲርሚዚ - 428]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከዝሁር ሶላት በፊት አራት ረከዓ ሱና ሶላቶችን፣ ከዝሁር በኋላም አራት ረከዓ ሱና ሶላቶችን የሰገደ፣ የዘወተረና የተጠባበቀን ሰው አላህ በርሱ ላይ እሳትን እርም እንደሚያደርግ አበሰሩ።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ከዝሁር በፊትም አራት ከዝሁር በኋላም አራት ረከዓዎችን መጠባበቅ ተወዳጅ እንደሆነ እንረዳለን።
  2. ከግዴታ ሶላት በፊት ቀብሊያ ሱናዎችን መስገድ በርካታ ጥበቦች አሉት። ከነርሱም መካከል: ወደ ግዴታ ከመግባት በፊት የሰጋጁን ነፍስ ለአምልኮ ያዘጋጃል። ከበዕዲያ ሱና ጥበብ መካከል ደግሞ የግዴታ ሶላትን ጉድለት መጠገን አንዱ ነው።
  3. ከግዴታ ሶላት በፊትና ኋላ የሚሰገዱ ሱና ሶላቶች ትልቅ ጥቅም አላቸው። ምንዳን ይጨምራሉ፤ ወንጀልን ያስምራሉ፤ ደረጃንም ከፍ ያደርጋሉ።
  4. ይህ ሐዲሥ ላይ የተጠቀሰውን የመሰለ ቃልኪዳን ያዘሉ ሐዲሦች ላይ የአህሉ ሱናዎች መርህ በተውሒድ ላይ በሞተ ላይ ነው የሚተረጉሙት። የተፈለገበትም በእሳት ውስጥ አለመዘውተር ነው። የተውሒድ ሰው ሆኖም ወንጀል የሚሰራ ሰው ለቅጣት የተገባ ቢሆንም ነገር ግን ቢቀጣ ራሱ እሳት ውስጥ አይዘወትርም።