عَنْ عُبَادَةَ بْنِ الصَّامِتِ رضي الله عنه أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«لَا صَلَاةَ لِمَنْ لَمْ يَقْرَأْ بِفَاتِحَةِ الكِتَابِ».

[صحيح] - [متفق عليه]
المزيــد ...

ከዑባዳህ ቢን ሷሚት (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል:
"የመጽሐፉን መክፈቻ (ፋቲሓን) ያላነበበ ሰው ሶላት የለውም።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari and Muslim]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የፋቲሓን ምዕራፍ በመቅራት ካልሆነ በቀር ሶላት ትክክለኛ እንደማትሆን ገለፁ። ፋቲሓ በሁሉም ረከዓዎች ከሚደረጉ የሶላት ማእዘናት መካከል አንዷ ናት።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ሩስያኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ፋቲሓን መቅራት እየቻለ ፋቲሓን ከመቅራት ፋንታ ሌላ ምእራፍ መቅራት አያብቃቃም።
  2. አውቆም ሆነ ሳያውቅ ወይም ረስቶ ፋቲሓ ያልተቀራበት ረከዓ የተበላሸ መሆኑን እንረዳለን። ምክንያቱም ፋቲሓ የሶላት ማእዘን ናት። ማእዘን ደግሞ በማንኛውም ሁኔታ ላይ ቢሆን አይወድቅም።
  3. ተከታይ የሆነ ሰው ኢማሙን ሩኩዕ ላይ ቢደርስበት ፋቲሓን የመቅራት ግዴታው ይነሳለታል።