+ -

عَنِ النَّوَّاسِ بْنِ سِمْعَانَ الْأَنْصَارِيِّ رضي الله عنه قَالَ:
سَأَلْتُ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ عَنِ الْبِرِّ وَالْإِثْمِ، فَقَالَ: «الْبِرُّ حُسْنُ الْخُلُقِ، وَالْإِثْمُ مَا حَاكَ فِي صَدْرِكَ، وَكَرِهْتَ أَنْ يَطَّلِعَ عَلَيْهِ النَّاسُ».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 2553]
المزيــد ...

ከነዋስ ቢን ሰምዓን አልአንሷሪይ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ:
«የአላህን መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ስለበጎ ተግባርና ስለወንጀል ጠየቅኳቸው። እርሳቸውም " በጎ ተግባር ማለት መልካም ስነምግባር ነው። ወንጀል ማለት በልብህ ውስጥ የተጣረጠርከውና (የተመላለሰ) ሰዎች ማወቃቸውን የጠላኸው ነገር ነው።" አሉኝ።»

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2553]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ስለበጎ ተግባርና ስለወንጀል ተጠየቁ። እርሳቸውም እንዲህ አሉ:
የበጎ ተግባር ትልቁ ነገር ከአላህ ጋር እርሱን በመፍራት፤ ከፍጡራን ጋር ደግሞ የሚያደርሱብንን አዛ (ችግር) በመቻል፣ ቁጣን በመቀነስ፣ ፊትን በመፍታት፣ ንግግርን በማሳመር፣ ዝምድናን በመቀጠል፣ በመታዘዝ፣ በመራራት፣ በጎ በመስራት፣ መልካም ቤተሰብና ባልደረባ በመሆን መልካም ስነምግባርን መላበስ ነው።
ወንጀል ማለት ደግሞ ልብህ ለርሱ ሳይከፈት ነፍስህ ውስጥ የተመላለሰ፣ የከነከነህ አሻሚ ነገር ነው። ስትሰራው ወንጀል ይሆን እያልክ ቀልብህ ውስጥ ጥርጣሬ የሚከሰትበትና የምትፈራው፣ ፀያፍ ስለሆነም አርአያ የሚሆኑ፣ ታላላቅና የተሟላ ስብዕና ያላቸው ሰዎች ፊት ጉዳዩ እንዲታወቅብህ የማትፈልገው ነው። ይህም ነፍስ በተፈጥሮዋ ሰዎች መልካም ስራዋን እንዲያውቁላት ነው የምትፈልገው። አንዳንድ ስራዋ መውጣቱን ከጠላች ግን ያ ስራ ወንጀል ነውና ምንም መልካም የለውም።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. በመልካም ስነምግባር ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን። መልካም ስነምግባር ከትላልቅ የበጎ ተግባር ጉዳዮች መካከል አንዱ ነውና።
  2. እውነትና ጥመት በአማኝ ላይ ምንም አሻሚ አይሆኑበትም። ይልቁንም ልቡ ውስጥ ባለ ብርሃን አማካኝነት እውነትንም ያውቀዋል፤ ከጥመትም ይሸሻል ያወግዛል።
  3. ከወንጀል ምልክቶች መካከል የልብ መከንከንና መመላለስ፣ ሰዎች ማወቃቸውንም መጥላትህ ነው።
  4. ሲንዲይ እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ የሚያጠነጥነው ሰዎች ከሁለት ነገሮች አንዱን ትክክል ለይተው የማያቁት በሆነ አሻሚ ጉዳይ ላይ ነው። ያለበለዚያማ በሸሪዓ ትእዛዝ መጥቶበት ከዚህ በጎ ተግባር የሚቃረን በዛ ጉዳይ ሌላ ማስረጃ ግልፅ ካልሆነለት፤ ልክ እንደዚሁ በተከለከሉ ወንጀሎች ዙሪያም በተቃራኒ ክልክልነቱን የሚቃረን ማስረጃ ከሌለ በነዚህ ጉዳይ ቀልብን መጠየቅና መረጋጋቷን ማጣራት ምንም አያስፈልግም።"
  5. ሐዲሡ የሚመለከተው የንፁህ ተፈጥሮ ባለቤቶችን ነው እንጂ ከስሜቱ ጋር የተጣጣመውን ካልሆነ በቀር መልካምን በመልካምነቱ መጥፎን በመጥፎነቱ የማያውቅ የተቀለበሰ ቀልብ ባለቤትን አይመለከተውም።
  6. ጢቢይ እንዲህ ብለዋል: "በተለያዩ ሐዲሦች በጎ ተግባር በብዙ ትርጉሞች ተተርጉሟል። አንድ ቦታ ላይ ነፍስ ወደርሱ የተረጋጋችበት፣ ቀልብም ወደርሱ የሰከነችበት ብለው ተርጉመውታል፤ አንድ ቦታ ላይ ደግሞ በኢማን ተርጉመውታል፤ በአንድ ቦታ ላይ ደግሞ ወደ አላህ የሚያቀርብክ ነገር ብለው ተርጉመውታል፤ እዚህ ሐዲሥ ውስጥ ደግሞ በመልካም ስነምግባር ተርጉመውታል። መልካም ስነምግባርም: ጉዳትን በመቻል፣ ቁጣን በመቀነስ፣ ፊትን በመፍታት፣ ንግግርን በማሳመር ተተርጉሟል። ሁሉም ትርጓሜ ሀሳባቸው ተመሳሳይ ነው።"