عن عائشة رضي الله عنها قالت:
كَانَ النَّبِيُّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَذْكُرُ اللهَ عَلَى كُلِّ أَحْيَانِهِ.

[صحيح] - [رواه مسلم]
المزيــد ...

ከእናታችን ዓኢሻህ -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና- እንደተላለፈው እንዲህ አለች:
"ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በሁሉም ሁኔታቸው አላህን ያወሱ ነበር።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari as Mu‘allaq/hanging, with a decisive form]

ትንታኔ

የአማኞች እናት ዓኢሻህ -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና- ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አላህን በማውሳት ላይ እጅግ ጉጉ እንደነበሩና በሁሉም ወቅት፣ ስፍራና ሁኔታ ላይ ሆነውም አላህን ያወሱ እንደነበር ተናገረች።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ስፔንኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ታጋሎግ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ጀርመንኛ ጃፓንኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አላህን ለማውሳት ከትንሹም ሆነ ከትልቁ ሐደሥ መፅዳት መስፈርት አይደለም።
  2. ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም አላህን በማውሳት ላይ ዘውታሪ እንደነበሩ እንረዳለን።
  3. መፀዳዳትን በመሰለ አላህን ማውሳት በሚከለከልባቸው ሁኔታዎች ካልሆነ በስተቀር ነቢዩን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከመከተል አኳያ በሁሉም ሁኔታ ላይ አላህን ማውሳት በማብዛት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
ተጨማሪ