عَنِ الْبَرَاءِ رَضيَ اللهُ عنه قَالَ:
مَا رَأَيْتُ مِنْ ذِي لِمَّةٍ أَحْسَنَ فِي حُلَّةٍ حَمْرَاءَ مِنْ رَسُولِ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، شَعْرُهُ يَضْرِبُ مَنْكِبَيْهِ، بَعِيدَ مَا بَيْنَ الْمَنْكِبَيْنِ، لَيْسَ بِالطَّوِيلِ وَلَا بِالْقَصِيرِ.
[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح مسلم: 2337]
المزيــد ...
ከበራእ- አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፦
"ባለረዥም ፀጉር ሁኖ ቀያይ መስመር ያለበትን ጥቁር አለባሽ ልብስ የሚያምርበት ከአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) የበለጠ እጅግ ውብ ሰው አልተመለከትኩም። ፀጉራቸው ትከሻቸውን ይመታ ነበር። በሁለቱ ትከሻዎቻቸው መካከል መራራቅ አለ። ረጅምም አጭርም አይደሉም።"
[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2337]
በራእ ቢን ዓዚብ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ከአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) የበለጠ ከርዝመቱ የተነሳ ፀጉሩ ትከሻው ድረስ የደረሰና ቀያይ መስመሮች ያሉበት ጥቋቁር ሽርጥና ኩታ የለበሰ አንድም እጅግ ውብ ሰው አልተመከትኩም ብለው ተናገሩ። በተጨማሪም ከርሳቸው አካላዊ ተፈጥሮ መካከል በሁለቱ ትከሻዎቻቸው መካከል መራራቅ እንዳለ፣ ደረታቸው ሰፊና ቁመታቸው አጭርም ረጅምም ሳይሆን መካከለኛ ቁመት እንደሆነ ተናገሩ።