+ -

عَنْ أَبَي قَتَادَةَ رضي الله عنه أنَّهُ طَلَبَ غَرِيمًا لَهُ، فَتَوَارَى عَنْهُ ثُمَّ وَجَدَهُ، فَقَالَ: إِنِّي مُعْسِرٌ، فَقَالَ: آللَّهِ؟ قَالَ: آللَّهِ؟ قَالَ: فَإِنِّي سَمِعْتُ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ:
«مَنْ سَرَّهُ أَنْ يُنْجِيَهُ اللهُ مِنْ كُرَبِ يَوْمِ الْقِيَامَةِ فَلْيُنَفِّسْ عَنْ مُعْسِرٍ أَوْ يَضَعْ عَنْهُ».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 1563]
المزيــد ...

ከአቡ ቀታዳህ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: «አቡ ቀታዳህ አንድ ተበዳሪውን ሲፈልገው ከርሱ ተሸሸገ። ከዚያም አገኘው። ተበዳሪውም "እኔ ችግርተኛ ነኝ።" አለው። እርሱም "ወላሂ በል!" አለው። ተበዳሪውም "ወሏሂ!" አለ። አቡቀታዳም እንዲህ አለ: "እኔ የአላህን መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ:‐
‹‹ከትንሳኤ ቀን ችግሮች አላህ እንዲገላግለው ያስደሰተው ሰው ለችግርተኛ ፋታ ይስጥ ወይም ከርሱ ያቅልልለት።»

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 1563]

ትንታኔ

አቡቀታዳህ አልአንሷሪይ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ከርሱ ይደበቅ የነበረን ተበዳሪን ይፈልግ ነበርና አገኘው። ተበዳሪውም እንዲህ አለው "እኔ ችግርተኛ ነኝ። እዳህን የምከፍልበት ገንዘብም የለኝም።"
አቡቀታዳህም (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ገንዘብ እንደሌለው ምሎ እንዲነግረው ጠየቀው።
በሚናገረው ነገር እውነቱን እንደሆነም በአላህ ምሎ ነገረው።
አቡ ቀታዳህም (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ሲሉ እነደደሰማ ተናገረ:
አላህ ከትንሳኤ ቀን ችግሮችና ጭንቆች እንዲያድነው ያስደሰተው ሰው ከችግርተኛ ያቅልል። ይህም መክፈያ ጊዜውን በማዘግየትና በማርዘም ወይም የተወሰነውን እዳ ወይም ሁሉንም ይቅር በማለት ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የተቸገረ ሰው አቅም እስኪያገኝ ድረስ መጠበቅ ወይም የተወሰነውን ወይም ሁሉንም እዳ ይቅር ማለት እንደሚወደድ እንረዳለን።
  2. ከአንድ አማኝ ላይ የዱንያ ችግሮችን ያቀለለ ሰው አላህ ከርሱ ላይ የትንሳኤ ቀን ችግሮችን ያቀልለታል። ምንዳ የሚገኘው እንደ ስራው አይነት ነውና።
  3. መርህ: ግዴታዎች ከሱናዎች ይበልጣሉ። ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ሱናዎች ከግዴታዎች የሚበልጡበት ጊዜ አለ። ከችግርተኛ ላይ እዳን ማንሳት ትርፍ (ሱና) ነው። ችግርተኛን መታገስ፣ መጠበቅና አለመወትወት ግዴታ ነው። በዚህ ወቅት ሱናው ከግዴታው ይበልጣል።
  4. ሐዲሡ የሚመለከተው መክፈል ያልቻለ ችግርተኛን ነው። ይህ ተቀባይነት ያለው ምክንያት ነውና። ገንዘብ እያለው አውቆ ለሚያዘገይ ሰው ግን ከነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና "የሃብታምን (የአበዳሪን) እዳ ማዘግየት ግፍ (በደል) ነው" የሚል መጥቷል።
ተጨማሪ