+ -

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضيَ اللهُ عنهُ سمعتُ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يقولُ:
«أَلاَ إِنَّ الدُّنْيَا مَلْعُونَةٌ، مَلْعُونٌ مَا فِيهَا، إِلاَّ ذِكْرُ اللهِ وَمَا وَالاَهُ وَعَالِمٌ أَوْ مُتَعَلِّمٌ».

[حسن] - [رواه الترمذي وابن ماجه] - [سنن الترمذي: 2322]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: «የአላህ መልዕክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ ብለዋል፦
"አዋጅ! ዱንያ የተረገመች ናት። አላህን ማውሳት፣ አላህን ከማውሳት ጋር የተቆራኘ፣ ዐዋቂ (ዐሊም) ወይም ዕውቀት ፈላጊ ካልሆነ በቀር በዱንያ ውስጥ ያለውም የተረገመ ነው።"

[ሐሰን ነው።] - [ቲርሚዚና ኢብኑማጀህ ዘግበውታል።] - [ሱነን ቲርሚዚ - 2322]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- አላህን ማውሳት፣ አላህን ወደ ማውሳት የቀረበና የተቆራኘ ወይም የሸሪዓን ዕውቀት ለሰዎች የሚያስተምር አዋቂ ወይም የሸሪዓን እውቀት የሚማር ካልሆነ በቀር ዱንያና በውስጧ ያሉ ነገሮች ባጠቃላይ ከአላህ የሚያጠምዱና የሚያርቁ ስለሆኑ በአላህ የተጠሉ፣ የተወገዙ፣ የተተዉና ከአላህ የራቁ እንደሆኑ ተናገሩ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ዱንያን በጥቅሉ ከመርገም የሚከለክሉ ሐዲሦች ስለመጡ አጠቃልሎ መርገም አይፈቀድም። ነገር ግን ዱንያ ውስጥ ከአላህ የሚያርቅና እርሱን ከመገዛት የሚያጠምድ ነገርን ነጥሎ መርገም ይፈቀዳል።
  2. አላህን ከማውሳት ወይም አላህን ለማውሳት ምክንያትና አጋዥ ከሆኑ ነገሮች ውጪ ዱንያ ውስጥ ያሉ ነገሮች ሁሉ ጨዋታና ዛዛታ ናቸው።
  3. የእውቀት፣ የእውቀት ባለቤቶችና የእውቀት ፈላጊዎች ደረጃ መገለፁን ተመልክተናል።
  4. ኢብኑ ተይሚያህ እንዲህ ብለዋል: "ከዱንያ የሚወገዘው ያለአግባብ የተገኘ ሐራም ገንዘብ ወይም ሐላል ከሆነም ለማብዛትና ለመፎከር ተብሎ የተሰበሰበ፤ ለመፎካከርና ለመወዳደር ታስቦ የሚከማችን ገንዘብ ነው። ይህም የአይምሮ ባለቤቶች ዘንድ የተጠላ ገንዘብ ነው።"
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ