عَنِ الزُّبَيْرِ بْنِ العَوَّامِ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«لَأَنْ يَأْخُذَ أَحَدُكُمْ حَبْلَهُ، فَيَأْتِيَ بِحُزْمَةِ الحَطَبِ عَلَى ظَهْرِهِ، فَيَبِيعَهَا، فَيَكُفَّ اللَّهُ بِهَا وَجْهَهُ خَيْرٌ لَهُ مِنْ أَنْ يَسْأَلَ النَّاسَ أَعْطَوْهُ أَوْ مَنَعُوهُ».
[صحيح] - [رواه البخاري] - [صحيح البخاري: 1471]
المزيــد ...
ከዙበይር ቢን አልዓዋም -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው: ነቢዩ - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል:
"አንዳችሁ ሰዎች ሰጡትም ከለከሉት ሰዎችን ከሚለምን ይልቅ ገመዱን ይዞ በጀርባው እንጨት አስሮ እያመጣ በመሸጥ አላህ ፊቱን (ከመገረፍ) ቢጠብቅለት የተሻለ ነው።"
[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪ ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 1471]
ነቢዩ - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - ሰው ማንኛውንም ስራ መስራት እንዳለበትና ገመዱን ይዞ ጀርባው ላይ የሚሸከመውን እንጨት ሰብስቦ በገመዱ አስሮ በመሸጥ ካገኘው ገንዘብም መመገቡ ወይም መመፅወቱ ከሰዎችም መብቃቃቱና ከልመና ውርደት (በሰው ፊት ከመገረፍ) ፊቱን መጠበቁ ሰጡትም ከለከሉትም ሰዎችን ከመለመን የተሻለ እንደሆነ ገለፁ። ሰዎችን መለመን ውርደት ነው። አማኝ ደግሞ ቆፍጣና እንጂ ወራዳ አይደለም።