+ -

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«أَكْثِرُوا ذِكْرَ هَادمِ اللَّذَّاتِ» يَعْنِي الْمَوْتَ.

[حسن] - [رواه الترمذي والنسائي وابن ماجه] - [سنن ابن ماجه: 4258]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልዕክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ብለዋል:
"ጥፍጥናን ቆራጩን ማስታወስ አብዙ።" ሞትን ማለታቸው ነው።

[ሐሰን ነው።] - - [ሱነን ኢብኑ ማጀህ - 4258]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- የሰው ልጅ እርሱን ሲያስታውሰው የመጪው ዓለምን የሚያስታውስበትንና ለዱንያ ጥፍጥና በተለይ ደሞ ክልክል ለሆኑ መጣቀሚያዎች ያለውን ፍቅር ከቀልቡ የሚያጠፋለትን ሞትን አብዝቶ እንዲያስታውስ አነሳሱ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሞት የዱንያን ጥፍጥና ይቆርጣል። ነገር ግን አማኝ የሆነን ሰው ወደ መጪው አለም ጥፍጥና፣ ወደ ጀነት ደስታና በጀነት ውስጥ ወደሚገኝ ትልቅ መልካም ነገር ነው የምታሸጋግረው።
  2. ሞትንና ከሞት በኋላ ያለውን ህይወት ማስታወስ የተውበት፣ ከወንጀል የመውጣትና ለመጪው አለም የመዘጋጀት ሰበብ ነው።
ትርጉም: እንግሊዝኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ሲንሃላዊ ቬትናማዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ