عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ: مَا خَطَبَنَا نَبِيُّ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ إِلَّا قَالَ:
«لَا إِيمَانَ لِمَنْ لَا أَمَانَةَ لَهُ، وَلَا دِينَ لِمَنْ لَا عَهْدَ لَهُ».
[حسن لغيره] - [رواه أحمد] - [مسند أحمد: 12383]
المزيــد ...
ከአነስ ቢን ማሊክ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ ነቢይ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ሳይሉን አንድም ኹጥባ አያደርጉም ነበር:
"አማና (አደራ) የሌለው ሰው ኢማን የለውም፤ ቃልኪዳን የማያከብር የሆነ ሰው ሃይማኖት የለውም።"»
[Hasan/Sound by virtue of corroborating evidence] - [አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሙስነድ አሕመድ - 12383]
አነስ ቢን ማሊክ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ ብለው ተናገሩ: ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ኹጥባ ሲያደርጉ ወይም ሲመክሩ ሁለት ነገሮችን ሳይጠቅሱ የሚያልፉበት ጊዜ በጣም ጥቂት ጊዜያት ነው። የመጀመሪያው: አንድን አካል በገንዘብ ወይም በነፍስ ወይም በቤተሰብ ጉዳይ ነፍሱ ውስጥ ከዳተኝነት ያለችበት ሰው የተሟላ ኢማን የለውም። ሁለተኛው: ቃልኪዳንን የሚያፈርስ ሰው የተሟላ ሃይማኖት የለውም።