+ -

عَنْ سَلْمَانَ الْفَارِسِيِّ رَضيَ اللهُ عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«ثَلَاثَةٌ لَا يُكَلِّمُهُمُ اللَّهُ يَوْمَ الْقِيَامَةِ وَلَا يُزَكِّيهِمْ وَلَهُمْ عَذَابٌ أَلِيمٌ: أُشَيْمِطٌ زَانٍ، وَعَائِلٌ مُسْتَكْبِرٌ، وَرَجُلٌ جَعَلَ اللَّهَ لَهُ بِضَاعَةً، فَلَا يَبِيعُ إِلَّا بِيَمِينِهِ وَلَا يَشْتَرِي إِلَّا بِيَمِينِهِ».

[صحيح] - [رواه الطبراني] - [المعجم الصغير: 821]
المزيــد ...

ከሰልማን አልፋሪሲይ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ብለዋል:
"ሶስት አይነት ሰዎች አላህ የትንሳኤ ቀን አያናግራቸውም። ከወንጀላቸውም አያጠራቸውም። ለነርሱም አሳማሚ ቅጣት አላቸው። የሽማግሌ ዝሙተኛ፣ የድሃ ኩራተኛና አላህን ሸቀጡ ያደረገ ሰው ነው። ያለመሃላ አይሸጥም። ያለመሃላው አይገዛም።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [At-Tabaraani]

ትንታኔ

ነቢዩ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- የትንሳኤ ቀን ተውበት እስካላደረጉ ወይም አላህ ቅጣቱን ይቅር እስካላላቸው ድረስ ቅጣት ስለሚገባቸው ሶስት የሰዎች አይነት ተናገሩ። የመጀመሪያው ቅጣት: የትንሳኤ ቀን አላህ በጣም ስለሚቆጣባቸው አያናግራቸውም። ይልቁንም እነርሱን ችላ ይላል። ወይም በነርሱ ላይ መቆጣቱን የሚጠቁም የማያስደስታቸውን ንግግር ያናግራቸዋል። ሁለተኛው ቅጣት: አያጠራቸውም፣ በነርሱ ላይ አያወድስም፣ ከወንጀላቸውም አያጠራቸውም። ሶስተኛው ቅጣት: በመጪው አለም አሳማሚና ብርቱ ቅጣት አላቸው። እነዚህም ሰዎች: የመጀመሪያው: ዝሙት ላይ የሚወድቅ ያረጀ ሰውዬ ነው። ሁለተኛው: ገንዘብ የሌለው ድሃ ከመሆኑም ጋር ሰዎች ላይ ይኮራል። ሶስተኛው: ሲሸጥና ሲገዛ በአላህ መማል የሚያበዛ ሰው ነው። በዚህም የአላህን ስም ዝቅ ያደርጋል። የአላህን ስምም ገንዘብ ማግኛ ያደርገዋል።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ቃዲ ዒያድ የዚህን ከባድ ቅጣት ምክንያት ሲገልፁ እንዲህ ብለዋል: "የተጠቀሱት እያንዳንዳቸው ከወንጀሉ ጋር ቅርርብ የሌላቸው ከመሆናቸውም ጋር፣ የሚያስገድዳቸው ካለመኖሩም ጋርና፣ ወደ ወንጀሉ የሚገፋፋቸው ሳይኖር ነው ወንጀሉን የፈፀሙት። ማንም ሰው ወንጀልን ለመፈፀም በቂ ምክንያት ባይኖረውም ነገር ግን ወደዚህ ወንጀል የሚያስገድድና በተለምዶ የሚገፋፋ ነገር ሳይኖረው መስራቱ ትዕቢት፣ የአላህን ሐቅ አቅልሎ ማየትና ያለምንም ፍላጎት ወንጀልን አልሞ መስራት ይመስልበታል።"
  2. ዝሙት፣ ውሸትና ኩራት ከትላልቅ ወንጀል መሆኑን እንረዳለን።
  3. ኩራት ማለት: እውነትን መመለስና ፍጡራንን ማሳነስ ነው።
  4. ሲሸጥና ሲገዛ መሃላን አብዝቶ መጠቀም መከልከሉንና መሃላን በማክበርና የአላህን ስሞች በማክበር ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን። አላህ እንዲህ ብሏል::{አላህን ለመሃላዎቻችሁ ግርዶ አታድርጉ።} [አልበቀራህ:32]
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ