+ -

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه قَالَ:
قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «يَقُولُ اللهُ عَزَّ وَجَلَّ: أَنَا عِنْدَ ظَنِّ عَبْدِي، وَأَنَا مَعَهُ حِينَ يَذْكُرُنِي، فَإِنْ ذَكَرَنِي فِي نَفْسِهِ ذَكَرْتُهُ فِي نَفْسِي، وَإِنْ ذَكَرَنِي فِي مَلَإٍ ذَكَرْتُهُ فِي مَلَإٍ خَيْرٍ مِنْهُ، وَإِنِ اقْتَرَبَ إِلَيَّ شِبْرًا، تَقَرَّبْتُ إِلَيْهِ ذِرَاعًا، وَإِنِ اقْتَرَبَ إِلَيَّ ذِرَاعًا، اقْتَرَبْتُ إِلَيْهِ بَاعًا، وَإِنْ أَتَانِي يَمْشِي أَتَيْتُهُ هَرْوَلَةً».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح مسلم: 2675]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ:
«የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል "አላህ እንዲህ አለ: እኔ ባሪያዬ ባሰበኝ በኩል ነኝ። ባስታወሰኝም ጊዜ እኔ ከርሱ ጋር ነኝ። ለብቻው ካወሳኝ ለብቻዬ አወሳዋለሁ፤ በህብረት ካወሳኝ ደሞ ከርሱ የተሻለ በሆኑ ህብረቶች ዘንድ አወሳዋለሁ። አንድ ስንዝር ወደኔ ከቀረበ አንድ ክንድ ወደርሱ እቀርባለሁ። አንድ ክንድ ወደኔ ከቀረበ እጅ ሙሉ ወደርሱ እቀርባለሁ። እየተራመደ ወደኔ ከመጣ በሶምሶማ ወደርሱ እመጣለሁ።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2675]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አላህ እንዲህ ማለቱን ተናገሩ:
እኔ ባሪያዬ እኔን ባሰበኝ በኩል ነኝ። ባሪያዬ ስለኔ ባለው እሳቤ አስተናግደዋለሁ። ይህም ተስፋ በማድረግ፣ ይቅርታዬን በመመኘት ነው። መልካምም ሆነ ከዛ ውጪ ከኔ ተስፋ ያደረገውን ከኔ ያገኛል። እኔን ካወሳኝ በእዝነቴ፣ በመግጠም፣ በመምራት፣ በመጠበቅና በማገዝ ከርሱ ጋር እሆናለሁ።
ለብቻው ተገልሎ በ"ተስቢሕ"፣ በ"ተህሊል" ወይም በሌሎች ዚክሮች ካወሳኝ ለብቻዬ አወሳዋለሁ።
በህብረት ካወሳኝ እርሱ እኔን ካወሳበት ህብረት በተሻለና በበዛ ምርጥ ህብረት እርሱን አወሳዋለሁ።
ወደ አላህ የስንዝር ያህል ለተቃረበ ሰው አላህም ጨምሮ የክንድ ያህል ወደርሱ ይቀርባል።
ክንድ ያህል ወደርሱ ከተቃረበ አላህም ሁለት ክንድ የሚያህል ወደርሱ ይቀርባል።
እየተራመደ ወደ አላህ ከመጣ አላህም ወደርሱ በሶምሶማ ይመጣል።
አንድ ባሪያ አላህን በመታዘዝና ወደርሱ በመዞር የተቃረበ ጊዜ በሰራው ስራ ትይዩ ለመመንዳት ጌታም ወደርሱ መቃረብን ይጨምርለታል።
አንድ አማኝ ለጌታው ያለው ባርነት በተሟላ ቁጥር አላህም ወደርሱ ይቀርባል። የአላህ ስጦታና ምንዳ ከባሪያው ስራና ጥንካሬ የበለጠ ነው። ዋናው ፍሬ ሀሳብ በቁጥርም ሆነ ሁኔታ የአላህ ምንዳ ከስራ ታመዝናለች የሚለው ነው።
አማኝ የሆነ ሰው በአላህ ላይ ያለውን እሳቤ ያሳምራል። አላህን እስኪገናኝ ድረስም ይጨምራልም ይፈጥናልም።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ይህ ሐዲሥ ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከጌታቸው የሚያወሩት ሐዲሥ ሲሆን ሐዲሠል ቁድሲይ ወይም ሐዲሠል ኢላሂይ በመባልም ይጠራል። ይህም ቃሉም ሆነ ሀሳቡ ከአላህ የሆነ ሲሆን ነገር ግን ቁርአን የተለየበት የሆነውን ማንበቡ አምልኮ መሆኑ፣ ለርሱ ዉዹእ ማድረግ፣ አምሳያውን እንዲያመጡ መገዳደሩ፣ ተአምራዊነቱና የመሳሰሉት መለያዎች የሉትም።
  2. አጁርሪይ እንዲህ ብለዋል: «የሐቅ ባለቤቶች አላህን ነፍሱን በገለፀበት ነገር፣ መልክተኛው (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በገለፁበትና ሶሐቦች (ረዲየሏሁ ዐንሁም) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - በገለፁበት መልኩ አላህ ይገልፃሉ፤ ይህ ሀቁን የተከተሉና አዲስ ነገር ያልፈጠሩ ዑለማዎች መንገድ ነው።» ተጠናቀቀ። አህሉ ሱናዎች አላህ ለነፍሱ ያፀደቀውን ስሞችና ባህሪያቱን ሳያጣምሙ፤ ትርጉም አልባ ሳያደርጉ፤ አኳኋኑን ሳይገልፁና ሳያመሳስሉ ለአላህ ያፀድቃሉ። አላህ ከራሱ ላይ ውድቅ ያደረገውንም ነገር ውድቅ ያደርጋሉ። ማፅደቅም ሆነ ውድቅ ማድረግ ካልመጣበት ጉዳይም ዝም ይላሉ። አላህ እንዲህ ብሏል {የሚመስለው ምንም ነገር የለም። እርሱም ሰሚው ተመልካች ነው።}
  3. በአላህ ላይ መልካም ማሰብ የግድ ከተግባር ጋር መሆን አለበት። ሐሰኑል በስሪይ እንዲህ ብለዋል: "ሙእሚን በጌታው ላይ ያለውን እሳቤ ስላሳመረ ስራውንም አሳመረ፤ አመጸኛ ሰው ደግሞ በጌታው ላይ ያለውን እሳቤ መጥፎ ስላደረገ ስራውንም መጥፎ አደረገ።"
  4. ቁርጡቢይ እንዲህ ብለዋል: "(ባሪያዬ ስለኔ ያሰበኝ ዘንድ ነኝ።) በሚለው ትርጉም ዙሪያ ዱዓ በሚያደርግ ወቅት ምላሹን እንደሚያገኝ ማሰበ፣ በተውበት ወቅት የተውበቱን ተቀባይነት ማግኘት ማሰብ፣ በኢስቲግፋር ወቅት ምህረትን ማግኘት ማሰብ፣ መስፈርቱን አሟልቶ አምልኮ በሚፈፀም ወቅት የቃሉን እውነተኝነት አምኖ መመንዳትን ማሰብ ነው ተብሏል። ስለዚህም ማንኛውም ሰው አላህ እንደሚቀበለውና እንደሚምረው እርግጠኛ ሆኖ በርሱ ላይ ያለበትን ግዴታ ለመወጣት ሊጥር ይገባዋል። ይህም አላህ ቃል ስለገባለት ነው። እርሱም ቃል ኪዳኑን የሚያፈርስ አይደለም። አላህ እንደማይቀበለውና ስራው እንደማይጠቅመው ካመነ ወይም ካሰበ ይህ ከአላህ እዝነት ተስፋ መቁረጥ ነው። ይህም ከትላልቅ ወንጀሎች መካከል አንዱ ነው። በአንዳንድ የዚህ ሐዲሥ ዘገባዎች ላይ (ባሪያዬ በኔ ላይ የፈለገውን ያስብ!) በሚል እንደመጣው በዚህ እሳቤው ላይ የሞተ ሰው ወዳሰበው ነው የሚጠጋው። ወንጀልን ከማዘውተር ጋር ምህረትን ማሰብ ግን ይህ ግልፅ መሃይምነትና መሸወድ ነው።"
  5. አላህን በውስጥህና በምላስህ ባጠቃላይ ማውሳትን በማብዛት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን። በነፍሱና በቀልቡ አላህን ይፈራል፤ ልቅናውንና ሐቁን ያስታውሳል፤ ይከጅለዋል፤ ያልቀዋል፤ ይወደዋል፤ በርሱ ላይ ያለውን እሳቤ ያሳምራል፤ ለርሱም ስራውን ያጠራል። በምላሱም: "ሱብሓነሏህ"፣ "ወልሐምዱሊላህ"፣ "ወላኢላሃ ኢለሏህ"፣ "ወሏሁ አክበር"፣ "ወላሐውለ ወላቁወተ ኢላ ቢላህ" በማለት ይናገራል።
  6. ኢብኑ አቢ ጀምረህ እንዲህ ብለዋል፡ "እየፈራው ያወሳው ሰው ደህንነትን ይሰጠዋል ወይም ጭርታ ተሰምቶት ያወሳውንም ያፅናናዋል።"
  7. ስንዝር ማለት: መዳፋችንን በምንዘረጋ ወቅት ከትንሿ ጣት ጫፍ እስከ አውራ ጣት ጫፍ መካከል ያለው ርቀት ነው። ክንድ ማለት: ከመሃል ጣት ጫፍ እስከ ክርን አጥንት ድረስ ያለው ርቀት ነው። ሙሉ እጅ ማለት: የሰው ሁለቱም ክንዶችና ጡንቻዎችን ዘርግቶ ከደረቱ ስፋት ጋር ያለው ርዝመት ነው። ይህም አራት ክንድ ያህላል።
ተጨማሪ