عَنِ ‌ابْنِ عَبَّاسٍ رضي الله عنهما قَالَ:
تَوَضَّأَ النَّبِيُّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ مَرَّةً مَرَّةً.

[صحيح] - [رواه البخاري]
المزيــد ...

ከኢብኑ ዓባስ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ:
"ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አንድ አንድ ጊዜ ዉዱእ አደርገዋል።"

Sahih/Authentic. - [Al-Bukhari]

ትንታኔ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በአንድ አንድ ወቅቶች ዉዱእ ያደረጉ ጊዜ ሁሉንም የዉዱእ አካላቶቻቸው አንድ አንድ ጊዜ ብቻ ያጥቡ ነበር። ፊታቸውን ‐ መጉመጥመጥና ውሀውን ወደ አፍንጫ ውስጥ ስቦ መልሶ ማውጣትን ጨምሮ‐ ፣ ሁለት እጃቸውንና ሁለት እግራቸውን አንድ አንድ ጊዜ ያጥቡ ነበር። ይህም ዝቅተኛው የግዴታ መጠን ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ቦስንያኛ ባንጋሊኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ህንድኛ ቬትናማዊ ሲንሃላዊ ኡይጙራዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ማላያላምኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታሚልኛ ቦርምኛ ታይላንድኛ ቡሽትኛ አሳምኛ አልባንኛ السويدية الهولندية الغوجاراتية الدرية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አካላቶቻችንን ስናጥብ ግዴታ ያለብን አንድ ጊዜ ብቻ ነው። ከዚህ በላይ መጨመር ተወዳጅ ነው።
  2. በአንድ አንድ ወቅቶች ላይ አንድ አንድ ጊዜ ብቻ ዉዱእ ማድረግ የተደነገገ መሆኑን እንረዳለን።
  3. ጭንቅላትን በማበስ ዙሪያ የተደነገገው አንድ ጊዜ ብቻ ማበስ ነው።