+ -

عَنْ أَنَسٍ رَضيَ اللهُ عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«لَوْ كَانَ لِابْنِ آدَمَ وَادِيَانِ مِنْ مَالٍ لَابْتَغَى وَادِيًا ثَالِثًا، وَلَا يَمْلَأُ جَوْفَ ابْنِ آدَمَ إِلَّا التُّرَابُ، وَيَتُوبُ اللهُ عَلَى مَنْ تَابَ».

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح مسلم: 1048]
المزيــد ...

አነስ ቢን ማሊክ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንዳስተላለፉት እንዲህ ብለዋል: «የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል፦
"የአደም ልጅ ሁለት በገንዘብ የሞላ ሸለቆ ቢኖረው ኖሮ ሶስተኛ ሸለቆ ይመኛል። የአደምን ልጅ ሆድ ከአፈር በቀር የሚሞላው የለም። ወደ አላህ ተፀፅቶ በተመለሰ ሰው ላይም አላህ ተውበቱን ይቀበለዋል።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 1048]

ትንታኔ

ነቢዩ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - የአደም ልጅ በወርቅ የሞላ ሸለቆ ቢኖረው ኖሮ በተፈጥሮው ካለው ስግብግብነት አንፃር ሌሎች ሁለት ሸለቆዎችን ይመኝ ነበር። የአደም ልጅ ሙቶ ከርሱ በቀብሩ አፈር ካልሞላ በቀር ለዱንያ ስግብግብ ከመሆን አይወገድም።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. የሰው ልጅ ገንዘብንና ሌሎችንም ዱንያዊ መጣቀሚያ በማግበስበስ ላይ ያለውን ከፍተኛ ጉጉት ያስረዳናል።
  2. ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "ከዚህ ሐዲሥ ለዱንያ መጓጓት፣ ዱንያን ማብዛትና እርሷን መከጀል የተወገዘ መሆኑን እንረዳለን።"
  3. አላህ ከተወገዘ ባህሪ ተፀፅቶ የሚመለስን ሰው ተውበት ይቀበላል።
  4. ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ የብዙሃኑን የአደም ልጆች የዱንያ ጉጉት ነው የገለፀው ይህንንም (ተፀፅቶ ተውበት ባደረገ ሰው ላይ አላህም ተውበቱን ይቀበለዋል።) የሚለው የነቢዩ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና -ንግግር ያጠናክረዋል።"
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ