+ -

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رضي الله عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«أَيُّهَا النَّاسُ، إِنَّ اللهَ طَيِّبٌ لَا يَقْبَلُ إِلَّا طَيِّبًا، وَإِنَّ اللهَ أَمَرَ الْمُؤْمِنِينَ بِمَا أَمَرَ بِهِ الْمُرْسَلِينَ، فَقَالَ: {يَا أَيُّهَا الرُّسُلُ كُلُوا مِنَ الطَّيِّبَاتِ وَاعْمَلُوا صَالِحًا، إِنِّي بِمَا تَعْمَلُونَ عَلِيمٌ} [المؤمنون: 51] وَقَالَ: {يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا كُلُوا مِنْ طَيِّبَاتِ مَا رَزَقْنَاكُمْ} [البقرة: 172] ثُمَّ ذَكَرَ الرَّجُلَ يُطِيلُ السَّفَرَ أَشْعَثَ أَغْبَرَ، يَمُدُّ يَدَيْهِ إِلَى السَّمَاءِ: يَا رَبِّ، يَا رَبِّ، وَمَطْعَمُهُ حَرَامٌ، وَمَشْرَبُهُ حَرَامٌ، وَمَلْبَسُهُ حَرَامٌ، وَغُذِيَ بِالْحَرَامِ، فَأَنَّى يُسْتَجَابُ لِذَلِكَ؟».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 1015]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
"እናንተ ሰዎች ሆይ! አላህ መልካም (ጥሩ) ነውና ከመልካም (ከጥሩ) በቀር አይቀበልም። አላህ መልክተኞችን ባዘዘው ነገር አማኞችንም አዟል። አላህ እንዲህ ብሏል: {እናንተ መልክተኞች ሆይ! ከተፈቀዱት ምግቦች ብሉ። በጎ ስራንም ስሩ። እኔ የምትሰሩትን ሁሉ አዋቂ ነኝ።} [አልሙእሚኑን:51] እንዲህም ብሏል: {እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ከነዚያ ከሰጠናችሁ ጣፋጮችን ብሉ።} [አልበቀራህ: 172]" ቀጥለውም ጉዞ የሚያረዝም፣ ጨብራራ፣ ፊቱንና ልብሱን አቧራ ያለበሰው አንድ ሰውዬ አወሱ። እጁን ወደ ሰማይ እየዘረጋ: "ጌታዬ ሆይ! ጌታዬ ሆይ! እያለ ይለምናል። ምግቡ ሐራም ነው። መጠጡ ሐራም ነው። ልብሱ ሐራም ነው። በሐራም ነው የተገነባው። እንዴት ለርሱ ዱዓው ተቀባይነት ይኖረዋል?" አሉ።»

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 1015]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አላህ መልካም፣ ከጉድለትና ነውር የጠራና የፀዳ፣ በምሉዕነት የሚገለፅ መሆኑን ተናገሩ፤ ከተግባርም፣ ከንግግርና ከእምነትም መልካም የሆነውን እንጂ እንደማይቀበል ተናገሩ። እርሱም ለአላህ ጥርት ተደርጎ የተሰራና የነቢዩን (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና መመሪያ የተከተለ ስራ ነው። በዚህ ካልሆነ በቀርም ወደ አላህ መቃረብ አይገባም። ለአንድ አማኝ ስራው መልካም ከሚሆንበት ትላልቅ ነገሮች መካከል ምግቡ መልካም መሆኑ ነው። ይህም የተፈቀደውን መመገቡ ነው። በዚህም ስራው ይፀዳል። ስለዚህም የተፈቀደን በመብላትና መልካም በመስራት አላህ መልክተኞችን እንዳዘዘው ሁሉ አማኞችንም አዘዘ። አላህ እንዲህ አለ: {እናንተ መልክተኞች ሆይ! ከተፈቀዱት ምግቦች ብሉ። በጎ ስራንም ስሩ። እኔ የምትሰሩትን ሁሉ አዋቂ ነኝ።} እንዲህም አለ: {እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ከነዚያ ከሰጠናችሁ ጣፋጮችን ብሉ።}
ቀጥለው ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ምንም ያህል ተቀባይነትን የሚያስገኙ ግልፅ ሰበቦችን ቢፈፅም ስራን የሚያበላሽና ተቀባይነቱን የሚያሳጣ ከሆነው ሐራም ምግብ ከመብላት አስጠነቀቁ። ለዱዓ ተቀባይነትን ያስገኛሉ ከተባሉት ግልፅ ሰበቦች መካከልም:
የመጀመሪያ: እንደ ሐጅ፣ ጂሃድ፣ ዝምድናን መቀጠልና ከዚህም ውጪ ላሉ ነገሮች ለአምልኳዊ አላማዎች ጉዞን ማርዘም ነው።
ሁለተኛው: ባለማበጠር ምክንያት የፀጉሩ መበታተንና በአፈር (በአቧራ) ምክንያት የልብሱ ቀለምና የሰውነት መልኩ መለወጡ ነው። ይህም አስገዳጅ ችግር የገጠመው መሆኑ ነው።
ሶስተኛው: ወደ ሰማይ ዱዓ በማድረግ እጁን ከፍ ያደርጋል።
አራተኛው: ጌታዬ ሆይ! ጌታዬ ሆይ! እያለ ወደ አላህ በስሞቹ ይቃረባል፣ በዚህም ችክ ይላል።
ከነዚህ ለዱዓ ተቀባይነትን ከሚያስገኙ ምክንያቶች ጋር ሆኖም ግን ዱዓው አልተሰማም። ይህም ምግቡ፣ መጠጡና ልብሱ ሐራም ስለሆነና በሐራም ስለተገነባ ነው። ባህሪው ይህ የሆነ ሰው ተቀባይነት ማግኘቱም ሩቅ ነው። አላህስ እንዴት ዱዓውን ይቀበለዋል?

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ቡሽትኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية Oromisht
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. አላህ ዐዘ ወጀል በዛቱ፣ በባህሪው፣ በድርጊቱና በህግጋቶቹ ምሉዕ መሆኑን እንረዳለን።
  2. ስራን ለአላህ ዐዘ ወጀል በማጥራት ላይና ነቢዩን (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በመከተል ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  3. "አላህ መልክተኞችን ባዘዘው ነገር አማኞችንም አዟል።" ከሚለው የነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ንግግር ለስራ የሚያነሳሳን አገላለፅ መጠቀም እንደሚገባ እንረዳለን። አንድ አማኝ ይህ ነገር መልክተኞችም የታዘዙት ነገር መሆኑን ሲያውቅ ለመተግበር ይበራታልም ይነሳሳልም።
  4. ዱዓን ተቀባይነት ከሚያሳጡ ነገሮች መካከል ሐራም መብላት አንዱ ነው።
  5. ዱዓ ተቀባይነት እንዲኖረው ከሚያደርጉ ሰበቦች መካከል አምስት ነገሮች ይገኛሉ: አንደኛ: ጉዞ ማርዘም ነው። በጉዞ ውስጥ ዱዓ ተቀባይነት ከሚያስገኙ ሰበቦች መካከል ትልቁ ሰበብ የሆነው ስብር (በጣም መተናነስን) ማለትን አቅፏልና። ሁለተኛ: በጭንቅ ሁኔታ ላይ መሆን። ሶስተኛ: እጆችን ወደ ሰማይ መዘርጋት። አራተኛ: የአላህን ጌትነት ደጋግሞ በማውሳት አላህ ላይ ችክ ማለት ሲሆን ይህም ዱዓ ተቀባይነት ያስገኛል ከሚባሉት መካከል ትልቁ ሰበብ ነው። አምስተኛ: ምግብና መጠጥን ማሳመር ናቸው።
  6. መልካምና ሐላል መብላት ለመልካም ስራ ከሚያግዙ ምክንያቶች መካከል አንዱ ነው።
  7. ቃዲ እንዲህ ብለዋል: መልካም (ጥሩ) ማለት የቆሻሻ ተቃራኒ ነው። በዚህ ባህሪ የተገለፀው አሏህ ሲሆን የሚፈለገው እርሱ ከጉድለቶች የፀዳ መሆኑንና ከእንከኖች የጠራ መሆኑን ነው። የተገለፀው በጥቅሉ ባሪያ ሲሆን ደግሞ ከውዳቂ ስነምግባርና ከፀያፍ ተግባራት የፀዳ መሆኑንና ከዚህ ተቃራኒ የሆነን ማንነት የተላበሰ መሆኑን የሚገልፅ ነው። ገንዘብ ሲገለፅበት ደግሞ ገንዘቡ ሐላል መሆኑንና ከምርጥ ገንዘብ መካከል እንደሆነ የሚገልፅ ነው።
ተጨማሪ