+ -

عَنْ هِشَامِ بْنِ حَكِيمِ بْنِ حِزَامٍ رَضيَ اللهُ عنهما أَنَّهُ مَرَّ عَلَى أُنَاسٍ مِنَ الْأَنْبَاطِ بِالشَّامِ، قَدْ أُقِيمُوا فِي الشَّمْسِ، فَقَالَ: مَا شَأْنُهُمْ؟ قَالُوا: حُبِسُوا فِي الْجِزْيَةِ، فَقَالَ هِشَامٌ: أَشْهَدُ لَسَمِعْتُ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَقُولُ:
«إِنَّ اللهَ يُعَذِّبُ الَّذِينَ يُعَذِّبُونَ النَّاسَ فِي الدُّنْيَا».

[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 2613]
المزيــد ...

ከሂሻም ቢን ሐኪም ቢን ሒዛም -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላችውና- እንደተላለፈው: ሂሻም በሻም ውስጥ በሚገኙ ዐረብ ባልሆኑ ገበሬዎች ፀሐይ ላይ እንዲቆሙ በተደረጉ ሰዎች በኩል አለፈ። እርሱም: "ምን ሆነው ነው?" አለ። ሰዎችም "ግብር ባለመክፈላቸው ለቅጣት እዚሁ ታስረው ነው።" ብለው መለሱለት። ሂሻምም «የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ሲሉ እንደሰማው እመሰክራለሁ:
"እነዚያን በዱንያ ውስጥ ሰዎችን የሚቀጡን ሰዎች አላህ ይቀጣቸዋል።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2613]

ትንታኔ

ሂሻም ቢን ሐኪም ቢን ሒዛም -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላችውና- ዐረብ ባልሆኑ ገበሬዎች በኩል ሲያልፍ ከፀሐይ ሐሩር በታች እንዲቆሙ ተደርገው ተመለከተ። ስለ ሁኔታቸውም ጠየቀ። ይህ የተደረገባቸው ግብር መክፈል እየቻሉ ባለመክፈላቸው እንደሆነም ተነገረው። ሂሻምም -አላህ መልካም ሥራውን ይውደድለትና- ከአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ሲሉ እንደሰማው እመሰክራለሁ አለ: አላህ ያለ አግባብ በግፍ በዱንያ ውስጥ ሌሎችን የሚቀጡ ሰዎችን ይቀጣቸዋል።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ጂዝያ (ግብር) ማለት: የመጽሐፍ ሰዎች ሆነው አቅመ አዳም በደረሱና ሀብታም በሆኑ ወንዶች ላይ በሙስሊሞች አገር ስለሚኖሩና ስለተሰጣቸው ከለላ እንዲከፍሉ የሚመደብባቸው ገንዘብ ነው።
  2. ያለ ሸሪዓዊ አስገዳጅ ምክንያት ከሃዲን እንኳን ቢሆን ሰዎችን መቅጣት ክልክል እንደሆነ እንረዳለን።
  3. በዳዮች ለበደላቸው እንደተዛተባቸው እንረዳለን።
  4. የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ባልደረቦች በመልካም ማዘዝና ከመጥፎ መከልከልን እንዴት አጥብቀው ይተገብሩ እንደነበር እንረዳለን።
  5. ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ የሚተረጎመው ያለ አግባብ በመቅጣት ነው። እንደ ቂሷስ (የገደለን መግደል)፣ (ሑዱድ) የሸሪዓዊ መቀጮዎችን ማስፈፀም፣ ስርዓት ለማስያዝ መቅጣትና የመሳሰሉት አግባብ የሆኑ ቅጣቶችን መቅጣት ሐዲሡ ውስጥ አይካተትም።"
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ታጋሎግ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ