+ -

عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيِّ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أَنَّهُ قَالَ:
«لَا يَمْنَعَنَّ رَجُلًا مِنْكُمْ مَخَافَةُ النَّاسِ أَنْ يَتَكَلَّمَ بِالْحَقِّ إِذَا رَآهُ أَوْ عَلِمَهُ».

[صحيح] - [رواه الترمذي وابن ماجه وأحمد] - [مسند أحمد: 11403]
المزيــد ...

ከአቡ ሰዒድ አልኹድሪይ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል፦
"ከናንተ መካከል እውነታን ተመልክቶ ወይም አውቆ ከመናገር ማናችሁንም ቢሆን ለሰዎች ያለው ፍራቻ እንዳይከለክለው።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቲርሚዚ፣ ኢብኑ ማጀህና አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሙስነድ አሕመድ - 11403]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- በባልደረቦቻቸው መካከል ኹጥባ አደረጉ። ከመከሯቸው ጉዳዮችም አንዱ የትኛውም ሙስሊም እውነትን ተመልክቶ ወይም አውቆ ከመናገርና በርሱ ከማዘዝ ሰዎችንና ሀይላቸውን መፍራትና መስጋት እንዳይከለክለው ነው።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. እውነትን ግልፅ በማድረግና ሰዎችን ፍራቻ እውነትን ባለመሸሸግ ዙሪያ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  2. እውነትን መናገር ማለት በአነጋገር መንገዱ ስርአትን፣ ጥበብንና በመልካም መልኩ መገሰፅን አይተግብር ማለትን አያሲዝም።
  3. መጥፎን ማውገዝና ከአላህ ሐቅ ጋር ከሚጋጭ የሰዎች ጥቅም የአላህን ሐቅ ማስቀደም ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።
ትርጉም: እንግሊዝኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ሲንሃላዊ ቬትናማዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ