عَنْ حُذَيْفَةَ رَضيَ اللهُ عنهُ عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«إِنَّهَا سَتَكُونُ أُمَرَاءُ يَكْذِبُونَ وَيَظْلِمُونَ، فَمَنْ صَدَّقَهُمْ بِكَذِبِهِمْ وَأَعَانَهُمْ عَلَى ظُلْمِهِمْ فَلَيْسَ مِنَّي، وَلَسْتُ مِنْهُ، وَلَا يَرِدُ عَلَيَّ الْحَوْضَ، وَمَنْ لَمْ يُصَدِّقْهُمْ بِكَذِبِهِمْ وَلَمْ يُعِنْهُمْ عَلَى ظُلْمِهِمْ فَهُوَ مِنِّي، وَأَنَا مِنْهُ، وَسَيَرِدُ عَلَيَّ الْحَوْضَ».
[صحيح] - [رواه أحمد] - [مسند أحمد: 23260]
المزيــد ...
ከሑዘይፋህ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ብለዋል:
"እነሆ የሚዋሹና ግፈኛ የሆኑ መሪዎች ይመጣሉ። ውሸታቸውን አምኖ የተቀበለና በበደላቸው ላይ ያገዛቸው እርሱም ከኔ አይደለም። እኔም ከርሱ አይደለሁም። ወደኔ ምንጭም (ወደ ሐውድ) አይመጣም። የነርሱን ውሸት አምኖ ያልተቀበለና በበደላቸውም ላይ ያላገዛቸው ሰው ደሞ እርሱ ከኔ ነው። እኔም ከርሱ ነኝ። ወደኔ ምንጭ (ሐውድም) ይመጣል።"
[ሶሒሕ ነው።] - [አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሙስነድ አሕመድ - 23260]
ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እርሳቸው ከሞቱ በኋላ ሲናገሩ የሚዋሹ፣ የማይሰሩትን የሚናገሩና በፍርዳቸው የሚበድሉ መሪዎች በሰዎች ላይ እንደሚሾሙ፤ ወደነርሱ ስራ ገብቶ ውሸታቸውን አምኖ የተቀበለ ወይም ወደነርሱ ለመቃረብ በሚልና እነርሱ ዘንድ ያለውን በመከጀል ለነርሱ የሚመቻቸውን ፈትዋ እንደመስጠት የመሰለ በሚሰሩት ወይም በሚናገሩት በደል ላይ ያገዛቸው እኔ ከርሱ የጠራሁ ነኝ። እርሱም ከኔ አይደለም። እኔም ከርሱ አይደለሁም። የትንሳኤ ቀንም የከውሠርን ምንጭ ሳጠጣ ወደኔ አይመጣም። ወደነርሱ ተግባር ያልገባ፤ ውሸታቸውን ያልተቀበለና በበደላቸው ላይም ያላገዛቸው እርሱ ከኔ ነው። እኔም ከርሱ ነኝ። የትንሳኤ ቀንም ወደ (ሐውድ) ምንጬ ይመጣል ብለው ተናገሩ።