عَنْ أُمَيْمَةَ بِنْتِ رُقَيْقَةَ رضي الله عنها أَنَّهَا قَالَتْ:
أَتَيْتُ النَّبِيَّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ فِي نِسْوَةٍ مِنَ الْأَنْصَارِ نُبَايِعُهُ، فَقُلْنَا: يَا رَسُولَ اللَّهِ، نُبَايِعُكَ عَلَى أَلَّا نُشْرِكَ بِاللَّهِ شَيْئًا، وَلَا نَسْرِقَ، وَلَا نَزْنِيَ، وَلَا نَأْتِيَ بِبُهْتَانٍ نَفْتَرِيهِ بَيْنَ أَيْدِينَا وَأَرْجُلِنَا، وَلَا نَعْصِيَكَ فِي مَعْرُوفٍ، قَالَ: «فِيمَا اسْتَطَعْتُنَّ، وَأَطَقْتُنَّ» قَالَتْ: قُلْنَا اللَّهُ وَرَسُولُهُ أَرْحَمُ بِنَا، هَلُمَّ نُبَايِعْكَ يَا رَسُولَ اللَّهِ، فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «إِنِّي لَا أُصَافِحُ النِّسَاءَ، إِنَّمَا قَوْلِي لِمِائَةِ امْرَأَةٍ كَقَوْلِي لِامْرَأَةٍ وَاحِدَةٍ، أَوْ مِثْلُ قَوْلِي لِامْرَأَةٍ وَاحِدَةٍ».
[صحيح] - [رواه الترمذي والنسائي وابن ماجه] - [سنن النسائي: 4181]
المزيــد ...
ከኡመይማህ ቢንት ሩቀይቃህ ረዺየሏሁ ዐንሃ - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው እንዲህ አለች:
«ነቢዩን ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ቃል ልንጋባ ከተወሰኑ የአንሷር ሴቶች ጋር ሆኜ መጣሁ። እንዲህም አልናቸው: "የአላህ መልክተኛ ሆይ! በአላህ ላይ አንዳችንም ላናጋራ፤ ላንሰርቅ፤ ዝሙትን ላንሰራ፤ በእጆቻችንና በእግሮቻችን መካከል የምንቀጥፈውን ቅጥፈት ላንፈፅም፤ በመልካም ጉዳይም ላናምፅዎት ቃል እንጋባዎ" እርሳቸውም: "በቻላችሁት ጉዳዮችና አቅማችሁ በሚፈቅደው ጉዳዮች ቃል ተጋባኃችሁ!" አሉን። እኛም "አላህና መልክተኛው ለኛ የበለጠ አዛኝ ናቸው። የአላህ መልክተኛ ሆይ! ኑ እጅዎን ይዘርጉ ቃል እንጋባዎ።" አልን። የአላህ መልክተኛም ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- "እኔ ሴቶችን አልጨብጥም። ለመቶ ሴቶች የምናገረው ቃል ለአንዲ ሴት እንደምናገረው ነው። ወይም ልክ ለአንድ ሴት እንደምናገረው ነው።" አሉ።»
[ሶሒሕ ነው።] - - [ሱነኑ ነሳኢይ - 4181]
ኡመይማህ ቢንት ሩቀይቃህ ረdiየሏሁ ዐንሃ - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተናገረችው እርሷ ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ዘንድ ከተወሰኑ የአንሷር ሴቶች ጋር ሆና በአላህ ላይ አንዳችንም ላያጋሩ፤ ላይሰርቁ፤ ዝሙት ላይሰሩ፤ በእጆችና በእግሮች መሃል የሚቀጥፉትን ላይፈፅሙ፤ በመልካም ነገር ላይ እርሳቸውን ላያምፁ ከርሳቸው ጋር ቃል ልትጋባ መጣች። ነቢዩም ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ አሉ: "በቻላችሁትና አቅማችሁ በሚፈቅዱ ጉዳዮች ላይ ቃል ተጋባኋቹህ።" እኛም: "አላህና መልክተኛው ለኛ የበለጠ አዛኝ ናቸው። የአላህ መልክተኛ ሆይ! ከወንዶች ጋር ቃል ሲጋቡ እንደሚፈፅሙት ኑ እጅዎን ይዘርጉና በመጨባበጥ ቃል እንጋባዎ።" አልን። እርሳቸውም እንዲህ አሉ: "እኔ ሴቶችን አልጨብጥም። ለመቶ ሴቶች የምናገረውና ቃል የምጋባው ለአንድ ሴት እንደምጋባው ነው።"