عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ عَنِ النَّبِيِّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ:
«أَسْرِعُوا بِالْجِنَازَةِ، فَإِنْ تَكُ صَالِحَةً فَخَيْرٌ تُقَدِّمُونَهَا، وَإِنْ يَكُ سِوَى ذَلِكَ، فَشَرٌّ تَضَعُونَهُ عَنْ رِقَابِكُمْ».
[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 1315]
المزيــد ...
ከአቡ ሁረይራ ረዺየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ብለዋል:
"ጀናዛን ፈጠን ብላችሁ ቅበሩ። ጀናዛው መልካም ከሆነ ወደ መልካም ነገር ማስቀደም ነው። ከዛ ውጪ ከሆነ ደግሞ መጥፎ ነገር ነው ከትከሻችሁ ማላቀቅ ነው።"
[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 1315]
ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ጀናዛን ለቀብር ማሰናዳት፣ ጀናዛው ላይ መስገድና መቅበር በፍጥነት እንዲከናወን አዘዙ። ጀናዛው መልካም ከሆነ ወደ መልካሙ የቀብር ፀጋ እያስቀደማችሁት ነው፤ ከዛ ውጪ ከሆነ ደግሞ መጥፎን ነገር ከትከሻችሁ እየተላቀቃችሁ ነው አሉ።