عن ابن عمر رضي الله عنهما:
أَنَّ رَسُولَ اللهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ نَهَى عَنِ الْقَزَعِ.

[صحيح] - [متفق عليه] - [صحيح البخاري: 5921]
المزيــد ...

ከኢብኑ ዑመር -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው:
"የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ፀጉርን አንዱን ተላጭቶ አንዱን ትቶ ከመቆረጥ ከልክለዋል።"

[ሶሒሕ ነው።] - [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ አልቡኻሪ - 5921]

ማብራሪያ

ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም የጭንቅላት ፀጉርን አንዱን ተላጭቶ አንዱን ትቶ ከመቆረጥ ከለከሉ።
ክልከላው ልጅም አዋቂም ወንዶችን የሚያጠቃልል ነው። ሴት ግን የጭንቅላት ፀጉሯን መላጨት አይፈቀድላትም።

ከሐዲሡ የሚቀሰሙ ቁምነገሮች

  1. ኢስላማዊ ሸሪዐ ለሰው ልጅ አካላዊ መገለጫም ትኩረት መስጠቱን እንረዳለን።
ትርጉሞችን አሳይ
ቋንቋ: الإنجليزية الأوردية الإسبانية ተጨማሪ (63)