+ -

عن جابر رضي الله عنهما قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«لن يدخلَ النارَ رجلٌ شَهِد بدرًا والحُدَيْبِيَة».

[صحيح] - [رواه أحمد، وأصله في صحيح مسلم] - [مسند أحمد: 15262]
المزيــد ...

ከጃቢር ቢን ዐብደላህ ረዲየሏሁ ዐንሁማ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ብለዋል:
"በድርና ሑደይቢያ ላይ የተሳተፈ ሰው እሳት አይገባም።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሙስነድ አሕመድ - 15262]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- በሂጅራ በሁለተኛው ዓመት የተካሄደችውን የበድር ዘመቻ ከነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ጋር ሆኖ ለመዋጋት የተሳተፈና በስድስተኛው አመተ ሂጅራ የተከሰተችውን የውዴታው ቃልኪዳን የነበረበትን የሑደይቢያን ስምምነት የተሳተፈ ሰው እሳት እንደማይገባ ተናገሩ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ይህ ሐዲሥ የበድርና የሑደይቢያ ተሳታፊዎችን ደረጃ ያስረዳናል። እነርሱም እሳት አይገቡም።
  2. አላህ እነርሱን ከበዳይነት (ሊጠብቃቸው) ኃላፊነት እንደወሰደላቸው፤ በኢማን ላይ መሞትን እንደሚገጥማቸው፤ የእሳት ቅጣት ሳይነካቸውም ጀነት እንደሚያስገባቸው መገለፁን እንረዳለን። ይህም አላህ ለሻው የሚሰጠው የአላህ ችሮታ ነው። አላህ የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው።
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ
ተጨማሪ