+ -

عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ رَضيَ اللهُ عنهُما قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«مَا أَسْكَرَ كَثِيرُهُ فَقَلِيلُهُ حَرَامٌ».

[حسن] - [رواه أبو داود والترمذي وابن ماجه وأحمد] - [سنن أبي داود: 3681]
المزيــد ...

ከጃቢር ቢን ዐብደሏህ ረዲየሏሁ ዐንሁማ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ፡ «የአሏህ መልዕክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ብለዋል፡
"ሲበዛ ያሰከረ ነገር ትንሹ ክልክል ነው።"

[ሐሰን ነው።] - [አቡዳውድ፣ ቲርሚዚ፣ ኢብኑማጀህና አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሱነን አቡዳውድ - 3681]

ትንታኔ

ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- አብዝቶ ሲወሰድ አይምሮን የሚያስወግድ ማንኛውም የሚጠጣ ወይም የሚበላ ነገር ሁሉ አይምሮን የሚያስወግድበትን ያህል መጠን የማይደርስ ትንሽ እንኳ መውሰድ ክልክል መሆኑን ገለፁ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሸሪዓ የሰዎችን አይምሮ እንደጠበቀ እንረዳለን።
  2. ወደ ክልክል የሚያደርሱ መንገዶችን መዝጋት የሚለው መርህ በትክክል የሚተገበር መሆኑን እንረዳለን። ይህም ሁሉንም ወደዚህ ቆሻሻ ነገር የሚያደርሱን መንገዶች ሁሉ በመዝጋት ነው።
  3. አስካሪን ነገር በጥቂቱ እንኳ መውሰድ ወደ ስካር መንገድ የሚያደርስ ስለሆነ መከልከሉን እንረዳለን።
  4. በትንሹም ሆነ አብዝቶ ቢወሰድ የማያሰክር ነገር ክልክል አለመሆኑን እንረዳለን።
ትርጉም: እንግሊዝኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ሲንሃላዊ ቬትናማዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ቴልጉ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ