+ -

عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضيَ اللهُ عنه قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ:
«مَنْ تَعَلَّمَ عِلْمًا مِمَّا يُبْتَغَى بِهِ وَجْهُ اللَّهِ عَزَّ وَجَلَّ لَا يَتَعَلَّمُهُ إِلَّا لِيُصِيبَ بِهِ عَرَضًا مِنَ الدُّنْيَا لَمْ يَجِدْ عَرْفَ الْجَنَّةِ يَوْمَ الْقِيَامَةِ» يَعْنِي رِيحَهَا.

[صحيح] - [رواه أبو داود وابن ماجه وأحمد] - [سنن أبي داود: 3664]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ ረዲየላሁ ዐንሁ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፦ «የአላህ መልዕክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ብለዋል፡
"የአላህ ፊት የሚፈለግበትን እውቀት የዱንያን ጥቅም ለማግኘት ካልሆነ በቀር ለሌላ ግብ የማይማረው ከሆነ የትንሳኤ ቀን የጀነትን ሽታ አያገኝም።"»

[ሶሒሕ ነው።] - [አቡዳውድ፣ ኢብኑ ማጀህና አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሱነን አቡዳውድ - 3664]

ትንታኔ

ነቢዩ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- በመሰረቱ የአላህ ውዴታ የሚፈለግበትን ሸሪዓዊ እውቀትን የተማረ ሰው ሲማረው ግን ገንዘብን ወይም ክብርን የመሰሉ የዱንያ መጣቀሚያና ዕጣፈንታዎችን ለማግኘት ካልሆነ በቀር የማይማረው የሆነ ሰው የትንሳኤ ቀን የጀነትን ሽታ አያገኝም አሉ።

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. እውቀትን በመፈለግ ወቅት ስራን ለአላህ ማጥራት ግዴታ መሆኑንና በዚህም ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
  2. ሸሪዓዊ እውቀትን ለይዩልኝ ወይም ለዱንያ ጥቅም በመገልገል ዙሪያ ከባድ ማስጠንቀቂያ መምጣቱንና ይህም ከትላልቅ ወንጀል የሚመደብ መሆኑን እንረዳለን።
  3. ለአላህ ብሎ እውቀትን የፈለገ ሰውና ያንን ተከትሎ ዱንያ ብትመጣለት እርሷን መጠቀም ይፈቀድለታልም ምንም አይጎዳውምም።
  4. ሲንዲይ እንዲህ ብለዋል: "ሐዲሡ ውስጥ "የጀነት ሽታን አያገኝም" መባሉ። ለርሱ ጀነት እርም መሆኗን ለማጋነን ነው። የአንድን ነገር ሽታዋንም የማያገኝ ሰው በርሷ ተጠቃሚነቱም የማይታሰብ ነው።"
  5. የአላህ ፊት የሚፈለግበትን እውቀት ስራ ለመቀጠሪያነት ወይም ለሌላ አላማ ብሎ የተማረ ሰው ከዚህ ወንጀሉ ወደ አላህ መመለስ አለበት። አላህ በተበላሸ ኒያው የተገኘውን ወንጀል ያብስለታል። እርሱ ጥራት ይገባውና የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው።
  6. ይህ ሸሪዓዊ እውቀትን ለሚቀስም ሰው ማስጠንቀቂያ ነው። እንደምህንድስና፣ ኬምስትሪና ሌሎችንም የዱንያ እውቀቶች ለዱንያ ብሎ የተማረ ግን በኒያው ያሰበውን ያገኛል።
ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ስፔንኛ ኢንዶኔዥያኛ ባንጋሊኛ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ሲንሃላዊ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ኩርዳዊ ሃውሳ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ ታይላንድኛ አሳምኛ الدرية الرومانية المجرية الجورجية الخميرية الماراثية
ትርጉሞችን ይመልከቱ