عَنْ أَبِي سَعِيدٍ رَضيَ اللهُ عنه:
أَنَّ جِبْرِيلَ أَتَى النَّبِيَّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَقَالَ: يَا مُحَمَّدُ اشْتَكَيْتَ؟ فَقَالَ: «نَعَمْ» قَالَ: «بِاسْمِ اللهِ أَرْقِيكَ، مِنْ كُلِّ شَيْءٍ يُؤْذِيكَ، مِنْ شَرِّ كُلِّ نَفْسٍ أَوْ عَيْنِ حَاسِدٍ، اللهُ يَشْفِيكَ بِاسْمِ اللهِ أَرْقِيكَ».
[صحيح] - [رواه مسلم] - [صحيح مسلم: 2186]
المزيــد ...
ከአቡ ሰዒድ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው:
«ጂብሪል ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ዘንድ መጣና እንዲህ አላቸው: "ሙሐመድ ሆይ! አመመህ እንዴ?" እርሳቸውም "አዎ" አሉ። እርሱም: "ቢስሚላሂ አርቂክ ሚን ኩሊ ሸይኢን ዩእዚክ ሚን ሸሪ ኩሊ ነፍሲን አው ዐይኒን ሓሲዲን አላሁ የሽፊክ ቢስሚላሂ አርቂክ" (ትርጉሙም: በአላህ ስም እጠብቅሃለሁ። ከሁሉም ከሚያውክህ ነገር ፣ ከሁሉም ክፉ ነፍስ ወይም ምቀኛ አይን አላህ እንዲፈውስህ በአላህ ስም እጠብቅሃለሁ።) አላቸው።»
[ሶሒሕ ነው።] - [ሙስሊም ዘግበውታል።] - [ሶሒሕ ሙስሊም - 2186]
መልአኩ ጂብሪል ዐለይሂ ሰላም ወደ ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - በመምጣት ጠየቃቸው: "ሙሐመድ ሆይ! በህመም ተጠቃህን?" እርሳቸውም: "አዎ" አሉ። ጂብሪልም ነቢዩን -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ በማለት ጥበቃ አደረገላቸው: "ቢስሚላሂ" በአላህ ስም ታግዤ "አርቂከ" እጠብቅሃለሁ። "ሚን ኩሊ ሸይኢን ዩእዚከ" ትንሽም ሆነ ትልቅ ከሚያውክህ ነገር ሁሉ እጠብቅሃለሁ። "ሚን ሸሪ ኩሊ ነፍሲን አው ዓይኒን ሓሲድ" ከሁሉም ክፉ ነፍስ ወይም ምቀኛ አይን እንዳያገኝህ እጠብቅሃለሁ። "አሏሁ የሽፊከ" አላህ ከሁሉም በሽታ እንዲፈውስህና እንዲጠብቅህ "ቢስሚላሂ አርቂከ" በአላህ ስም እጠብቅሃለሁ። ("ቢስሚላሂ አርቂክ" የሚለውን) ሁለቴ የደጋገመውና በርሱ ጀምሮ በርሱ ያጠናቀቀው ከአላህ ውጪ ማንም እንደማይጠቅም ለመጠቆም ነው።