عَنْ لَقِيطِ بْنِ صَبِرَةَ رَضيَ اللهُ عنه قَالَ:
كُنْتُ وَافِدَ بَنِي الْمُنْتَفِقِ -أَوْ فِي وَفْدِ بَنِي الْمُنْتَفِقِ- إِلَى رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، قَالَ: فَلَمَّا قَدِمْنَا عَلَى رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَلَمْ نُصَادِفْهُ فِي مَنْزِلِهِ، وَصَادَفْنَا عَائِشَةَ أُمَّ الْمُؤْمِنِينَ، قَالَ: فَأَمَرَتْ لَنَا بِخَزِيرَةٍ، فَصُنِعَتْ لَنَا، قَالَ: وَأُتِينَا بِقِنَاعٍ -وَالْقِنَاعُ: الطَّبَقُ فِيهِ تَمْرٌ- ثُمَّ جَاءَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَقَالَ: «هَلْ أَصَبْتُمْ شَيْئًا؟ أَوْ أُمِرَ لَكُمْ بِشَيْءٍ؟» قَالَ: قُلْنَا: نَعَمْ، يَا رَسُولَ اللَّهِ، قَالَ: فَبَيْنَا نَحْنُ مَعَ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ جُلُوسٌ، إِذْ دَفَعَ الرَّاعِي غَنَمَهُ إِلَى الْمُرَاحِ، وَمَعَهُ سَخْلَةٌ تَيْعَرُ، فَقَالَ: «مَا وَلَّدْتَ يَا فُلَانُ؟»، قَالَ: بَهْمَةً، قَالَ: «فَاذْبَحْ لَنَا مَكَانَهَا شَاةً»، ثُمَّ قَالَ: «لَا تَحْسِبَنَّ» وَلَمْ يَقُلْ: لَا تَحْسَبَنَّ «أَنَّا مِنْ أَجْلِكَ ذَبَحْنَاهَا، لَنَا غَنَمٌ مِائَةٌ لَا نُرِيدُ أَنْ تَزِيدَ، فَإِذَا وَلَّدَ الرَّاعِي بَهْمَةً، ذَبَحْنَا مَكَانَهَا شَاةً» قَالَ: قُلْتُ: يَا رَسُولَ اللَّهِ، إِنَّ لِي امْرَأَةً وَإِنَّ فِي لِسَانِهَا شَيْئًا -يَعْنِي الْبَذَاءَ- قَالَ: «فَطَلِّقْهَا إِذن»، قَالَ: قُلْتُ: يَا رَسُولَ اللَّهِ إِنَّ لَهَا صُحْبَةً، وَلِي مِنْهَا وَلَدٌ، قَالَ: «فَمُرْهَا» يَقُولُ: عِظْهَا، «فَإِنْ يَكُ فِيهَا خَيْرٌ فَسَتَفْعَلْ، وَلَا تَضْرِبْ ظَعِينَتَكَ كَضَرْبِكَ أُمَيَّتَكَ» فَقُلْتُ: يَا رَسُولَ اللَّهِ، أَخْبِرْنِي عَنِ الْوُضُوءِ، قَالَ: «أَسْبِغِ الْوُضُوءَ، وَخَلِّلْ بَيْنَ الْأَصَابِعِ، وَبَالِغْ فِي الِاسْتِنْشَاقِ إِلَّا أَنْ تَكُونَ صَائِمًا».
[صحيح] - [رواه أبو داود والترمذي والنسائي وابن ماجه] - [سنن أبي داود: 142]
المزيــد ...
ለቂጥ ቢን ሰቢራህ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላችውና- እንዲህ አሉ:
«ወደ አላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ከተላኩ የበኒ አልሙንተፊቅ ወይም በበኒ አልሙንተፊቅ ልዑክ ውስጥ ነበርኩ። የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ዘንድ ስንደርስ በቤታቸው አላገኘናቸውም ነበር። የአማኞች እናትን ዓኢሻን አገኘን። በስጋና ዱቄት የሚሰራ (ኸዚራ) የሚባል ምግብ እንዲሰራልን አዘዘች። ለኛም ተሰራልን። በጎድጓዳ ሳህንም ተምር መጣልን። ከዚያም የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - መጥተው እንዲህ አሉን "የሚቀመስ ነገር አገኛችሁ?" ወይም "የሚቀመስ ነገር ታዘዘላችሁ?" እኛም "አዎ የአላህ መልክተኛ ሆይ!" አልን። እኛ ከአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ጋር ተቀምጠን ሳለ የርሳቸው እረኛ ፍየሎቹን ወደ ማደሪያቸው ያስገባ ጀመር። ከርሱ ጋር የምትጮህ ግልገል ነበረች። እርሳቸውም "እከሌ ሆይ! አላራባህምን?" አሉት። እርሱም "ግልገል ናት።" አላቸው። እርሳቸውም "በርሷ ቦታ አንድ ፍየል እረድልና!" አሉት። ቀጥለውም "ለናንተ ብለን የምናርድላችሁ አድርጋችሁ እንዳታስቡ። እኛ መቶ ፍየል አለን። ከመቶ እንዲጨምር ስለማንፈልግ እረኛው አንድ ሲያራባ በርሷ ቦታ አንድ እናርዳለን።" አሉ። እኔም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! እኔ ምላሷ ላይ ችግር ያለባት ሚስት አለችኝ። ምን ይሻለኛል?" ብዬ ጠየቅኳቸው። እርሳቸውም "እንደዛ ከሆነ ፍታት" አሉኝ። እኔም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! እርሷ ከኔ ጋር የቆየ ቁርኝት አላት። ከርሷም ልጆች አሉኝ።" አልኳቸው። እርሳቸውም "ምከራት! ውስጧ መልካምነት ካለ ትታዘዝሃለች። ሚስትህን የባሪያ አመታት እንዳትመታ።" አሉኝ። እኔም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ስለ ዉዱእ ንገሩኝ።" አልኳቸው። እርሳቸውም "ዉዱእን አዳርሰህ አድርግ። በጣቶችህ መካከል ፈልፍል። ፆመኛ እስካልሆንክ ድረስም አፍንጫህ ውስጥ ውሃ ስትከት በደንብ አስገባ።" አሉኝ።»
[ሶሒሕ ነው።] - - [ሱነን አቡዳውድ - 142]
ለቂጥ ቢን ሰቢራህ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላችውና- ከህዝቦቹ ተመርጦ ከሌሎች ጋር ወደ አላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ከተላኩ የበኒ አልሙንተፊቅ ልዑክ ውስጥ እንደነበረ ተናገረ። እንዲህም አለ: በቤታቸው አላገኘናቸውም ነበር። የአማኞች እናትን ዓኢሻን -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና - አገኘን። በስጋና ዱቄት የሚሰራ (ሐሳእ) የሚባል ምግብ እንዲሰራልን አዘዘች። ለኛም ተሰራልን። በጎድጓዳ ሳህንም ተምር መጣልን። ከዚያም የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - መጥተው እንዲህ አሉን "የሆነ ምግብ ቀረበላችሁ?" እኛም "አዎ" አልን። ለቂጥ እንዲህ አለ: እኛ ከአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ጋር ተቀምጠን ሳለ የነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እረኛ ፍየሎቹን ወደ ማደሪያቸው ሊያስገባ እየነዳ አመጣቸው። ከርሱ ጋርም የምትጮህ የፍየል ግልገል ነበረች። እርሳቸውም "አላራባህምን?" አሉት። እርሱም "ሴት ግልገል ናት።" አላቸው። እርሳቸውም "በርሷ ቦታ አንድ የደረሰች ፍየል እረድልና!" አሉት። ቀጥለውም ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ አሉ: "ለናንተ ብለን ተጨናንቀን የምናርድላችሁ አድርጋችሁ እንዳታስቡ። እኛ መቶ ፍየል አለን። ከመቶ እንዲጨምር ስለማንፈልግ አንድ አዲስ ግልገል ሲወለድልን በርሷ ቦታ አንድ እናርዳለን።" አሉ። ለቂጥም እንዲህ አለ: "የአላህ መልክተኛ ሆይ! እኔ ምላሷ ላይ ጣጣ ያለባት አስከፊ ምላስ ያላት ሚስት አለችኝ። ከርሷ ጋር ምን ባደርግ ይሻለኛል?" ብዬ ጠየቅኳቸው። እርሳቸውም "እንደዛ ከሆነ ፍታት" አሉኝ። እኔም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! እርሷ ከኔ ጋር የቆየ ቁርኝት አላት። ከርሷም ልጆች አሉኝ።" አልኳቸው። እርሳቸውም "ምከራት! ውስጧ መልካምነት ካለ ምክርህን ትቀበልሃለች። ካልተቀበለች የማያቆስል ምት ምታት እንጂ ሚስትህን የባሪያ አመታት እንዳትመታ።" አሉኝ። ለቂጥም ቀጥሎ እንዲህ አላቸው "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ስለ ዉዱእ ንገሩኝ።" አላቸው። እርሳቸውም "ዉዱእህን ስታደርግ ዉዱእን አዳርሰህ አድርግ። ለሁሉም አካላትህ ሐቁን ስጥ። የዉዱእን ግዴታና ሱና ምንም አትተው። በእጅና እግር ጣቶችህ መካከል ከፋፍትና ፈልፍል። ውሃው ወደ ውስጥህ እንዳይገባ ጾመኛ እስካልሆንክ ድረስ አፍንጫህ ውስጥ ውሃ ስትስብ በደንብ አስገባ።" አሉኝ።