+ -

عن أبي هريرة رضي الله عنه قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم:
«مَلْعُون مَنْ أتَى امرأتَه في دُبُرِها».

[حسن] - [رواه أبو داود والنسائي في الكبرى وأحمد] - [سنن أبي داود: 2162]
المزيــد ...

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል: «የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል:
"ሚስቱን በመቀመጫዋ የተገናኛት ሰው የተረገመ ነው።"»

[ሐሰን ነው።] - [አቡዳውድ፣ ነሳኢ በኩብራ ውስጥ፣ አሕመድ ዘግበውታል።] - [ሱነን አቡዳውድ - 2162]

ትንታኔ

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ባል ሚስቱን በመቀመጫዋ በኩል መገናኘቱን ከለከሉ። ከአላህ እዝነት የተባረረና የተረገመ መሆኑንም ገለፁ። ከትላልቅ ወንጀሎች መካከል የሚመደብም ነው።

ትርጉም: እንግሊዝኛ የኡርዱ ቋንቋ ኢንዶኔዥያኛ ኡይጙራዊ ፈረንሳይኛ ቱርክኛ ሩስያኛ ቦስንያኛ ህንድኛ ቻይንኛ ፋርስኛ ቬትናማዊ ኩርዳዊ ፖርቹጋልኛ ስዋሒልኛ አሳምኛ الهولندية الغوجاراتية
ትርጉሞችን ይመልከቱ

ከሐዲሱ የምንጠቀማቸው ቁምነገሮች

  1. ሴቶችን በመቀመጫቸው በኩል መገናኘት ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
  2. ሚስትን ከመቀመጫዋ ውጪ ባለ አካሏ መጠቀም ይፈቀዳል።
  3. ሙስሊም የሆነ ሰው አላህ እንዳዘዘው ሚስቱን በብልቷ በኩል መገናኘት ነው ያለበት። በመቀመጫ በኩል መገናኘት ግን ተፈጥሮን መፃረር (ማበላሸት)፣ ዘርን ማባከን፣ ንፁህ ተፈጥሮ ያለበትን መፃረር፣ በጥንዶቹ ላይም ከመጠን ያለፈ ጉዳት የሚያደርስ ነው።